Articles

የጤና ሚኒስቴር፣ የክልል የጤና ቢሮዎች እና የተጠሪ ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች የጋራ መድረክ ተጀምሯል

JSC

በጋራ የውይይት መድረኩ መክፈቻ ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ እንደተናገሩት የጤናው ዘርፍ ከፍተኛ አመራሮች የጋራ መድረኩ በዘርፉ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት አፈጻጸምን፣ ተግዳሮቶችን እና የተገኙ ልምዶችን በጋራ ለመገምገምና የቀጣይ  አቅጣጫ ላይ ለመግባባት ይረዳል፡፡ 


የተለያየ ግጭት ያለባቸውን ሁሉንም አካባቢዎች በአግባቡ በመዳሰስ እና ሁሉም የኅብረተሰብ ክፍል አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያገኙ፣ በሆስፒታሎች እና በጤና ተቋማት አስፈላጊ ግብዓቶችን በማሟላት የተቋረጡ የሕክምና አገልግሎቶች መልሰው እንዲጀምሩ ማድረግ እንደሚገባ የገለፁት ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ ይህም በጋራ የውይይት መድረኩ በትኩረት የሚገመገም አጀንዳ አንዱ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

በአማራ እና አፋር ክልሎች ጉዳት ለደረሰባቸው የሆስፒታል ላብራቶሪዎችን መልሶ ለማቋቋም የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ ተደረገ 

donation

6.5 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ የላብራቶሪ ህክምና ቁሳቁስ ድጋፍን ያደረገው የኦሃዮ ስቴት ግሎባል ዋን ሄልዝ ሲሆን በጦርነት ጉዳት የደረሰባቸው የህክምና ተቋማትን መልሶ ለማቋቋም የሚውል መሆኑ ተገልጿል፡፡ 


የጤናው ዘርፍ በጦርነቱ ከፍተኛ ውድመት ያሰተናገደ ዘርፍ መሆኑን የገለጹት የጤና ሚኒስቴር ሚንስትር ዴዔታ ዶ/ር አየለ ተሸመ፤ የተደረገው ድጋፍ ያጋጠሙትን ችግሮች ለመቅረፍ የሚረዳ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ 


የላብራቶሪ ህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ የተደረገላቸው ተቋማት የተሟላ የህክምና አገልግሎት ለመስጠት እንዲችሉ እየተደረገ ያለውን ጥረት የሚደገፍ መሆኑን በመግለጽ ስለተደረገው ድጋፍ በጤና ሚኒስቴር፣ ድጋፍ በተደረገላቸው ተቋማት እና በተቋማቱ አገልግሎት በሚያገኙ ማህበረሰቦች ስም ምስጋና አቅርበዋል፡፡ 

የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት የቲቢ በሽታን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በጋራ ሊሰሩ ይገባል

EGAD

16ኛው አመታዊ የቲቢ ምርምር ጉባኤ ላይ ከተገኙ የአጎራባች ሃገራት ተወካዮችጋር የቲቢ በሽታን መከላከልና መቆጣጠር በተመለከተ የጎንዮሽ ውይይት ተካሂዷል።

አጎራባች ሀገራት በሚዋሰኑባቸው አከባቢዎች ተመሳሳይ ማህበረሰብ የሚገኝባቸው በመሆናቸው እና በተለይም አርብቶ አደር በሚበዛባቸው የምስራቅ አፍሪካ አጎራባች አከባቢዎች የቲቢ በሽታ ህክምናን ለመስጠትም ሆነ ክትትል ለማድረግ አዳጋች በመሆኑ ሃገራቱ በጋራ መስራታቸው ጠቀሜታው የጎላ ይሆናል።

በአጎራባች አከባቢዎች ያለው ነባራዊ ሁኔታን የሚያመለክት በቂ መረጃ አለመኖር እና የግብአት ውስንነት ማነቆ መሆኑን ተወካዮች አውስተው የምርምር ተግባራትን በስፋት መስራት፣ ትብብርን ማጠናከርና ለጉዳዩ ትኩረት እንዲሰጥ ከፍተኛ ሃላፊዎችን ማስገንዘብና የሚድያና ተግባቦት ፕላትፎርም ተፈጥሮ በትኩረት በጋራ መስራት አስፈላጊ እንደሆነ ጠቁመዋል።