በህግ ማስከበር እና በህልውና ዘመቻው አስተዋጽኦ ላበረከቱ የጤናው ዘርፍ አካላት ምስጋናና እውቅና ተሰጣቸው
በሃገራችን በተካሄደው በህግ ማስከበር እና በህልውና ዘመቻው ላይ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ጤና ተቋማት፣ ጤና ክብካቤ ባለሙያዎችና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጤና ሚኒስቴር እና በኢ.ፌ.ዲ.ሪ መከላከያ ሚኒስቴር በጋራ የተዘጋጀ የምስጋና የእውቅና መርሃ ግብር ተካሄደ፡፡
በፕሮግራሙ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር አብይ አህመድ ባደረጉት ንግግር የጤና ባለሙያዎችና የጤና ክብካቤ ሰራተኞች እንደ ሰው፣ እንደ ኢትዮጵያዊ እና እንደ ሃኪም ሶስት ማንነትን ተላብሳችሁ ለሰራችሁት ታላቅ ገድል ከፍተኛ ምስጋና ይገባችኋል ብለዋል፡፡