Articles

የአፍሪካ ህብረት ልማት ኤጀንሲ-ኔፓድ የሚኒስትሮች መድረክ  ለተዋልዶ ጤና ትኩረት በመስጠት ሁሉን አቀፍ የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን ማፋጠን እና የአፍሪካን ስነ-ህዝብ አቅም መጠቀም” በሚል መሪ ቃል ተካሂዷል፡፡ 

Dr Mekdes Daba

በመድረኩ  የተሳተፉ የአፍሪካ ሃገራት ሚኒስትሮች ልምድ የሚለዋወጡበት እና በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን መግባባት ላይ የሚደርሱበት መድረክ መሆኑን የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ በመድረኩ የመክፈቻ ንግግራቸው ያስረዱ ሲሆን፤ ጉባኤው በዋናነት የስነ-ተዋልዶ ጤና ላይ ትኩረቱን ማድረጉን ገልጸዋል፡፡ 


ኢትዮጵያ በስነ-ተዋልዶ ጤና ላይ ከፍተኛ ኢንቨስትመንት ማፍሰሷን ያስታወሱት ዶ/ር መቅደስ፤ በዚህም የእናቶች እና ህጻናት ህልፈትን መቀነስ መቻሉን እና አጠቃላይ የጤና ስርአትንም ማሻሻል መቻሉን አብራርተዋል፡፡ የአፍሪካ ሃገራት የሃገር ውስጥ ምርትን በማሳደግ አፍሪካ በጤና ዘርፍ እራሷን እንድትችል መስራት ይገባል ያሉት ሚኒስትሯ፤ ያጋጠሙ የፋይናንስ ክፍተቶችን የሃገር ውስጥ ሃብትን በማሳባሰብ እና ከአጋሮች ጋር በትብብር በመስራት መቅረፍ እንደሚገባ አክለዋል፡፡

ኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነው የሆስፒታል የአክሪዲቴሽን ስታንዳርድ(ደረጃ) ለህዝብ አስተያየት ክፍት ሆነ፡

የጤና ሚኒስቴር የጤና አገልግሎት ጥራት እና ደህንነት ለማረጋገጥ የጤና ተቋማት የአክሪዲቴሽን ስርዓት ማስፈፀሚያ ፍኖተ ካርታ ከኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት፤ የኢትዮጵያ አክሪዲቴሽን አገልግሎት ፤ የኢትዮጵያ የጤና ክብካቤ ፌዴሬሽንና አጋር አካላት እና ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በጋራ አዘጋጅቶ በትግበራ ላይ መሆኑ ይታወቃል፡፡

የጤና ተቋማት በሚሰጡት የጤና አገልግሎት በሃገር ዓቀፍ እና ዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ መሆን እንዲችሉ የኢትዮጵያ ሆስፒታሎች አገልግሎት አክሪዲቴሽን ስታንዳርድ/ደረጃ/ ከኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር አዘጋጀቶ ረቂቅ ሰነድ ለህዝብ አስተያየት በይፋ ክፍት ያደረገ ሲሆን እርስዎም ሰነዱን ከዚህ በታች ከተቀመጠዉ ድህረ -ገጽ በማዉረድ አስተያየትዎን በቀረበዉ ቅፅ መሰረት መጠይቁን በአግባቡ በመሙላት አስተያየት እንዲሰጡ ተጋብዘዋል፡፡

ለሚሰጡት ገንቢ አስተያየትም በተገልጋይ ማህበረሰባችን ስም ከወዲሁ እናመሰግናለን፡፡

ኦንኮሳርኪያሲስ በሽታን ለማጥፋት የተቋቋመ የኤክስፐርቶች አማካሪ ኮሚቴ 11ኛ አመታዊ ጉባኤውን አካሄደ

ኦንኮሳርኪያሲስ የቆዳና የአይን ችግር የሚያስከትል በሽታ ነው። በሽታው ኦንኮሰርካ ቮልቮሉስ በሚባል ኢንፌክሽን ምክንያት የሚከሰት ሲሆን፤ ምልክቶቹም ከባድ የማሳከክ ስሜት፣ ከቆዳ ስር ያሉ እብጠቶች እና ዓይነ ስውርነት ናቸው። እንደ DEET ያሉ ነፍሳትን የሚከላከሉ መድኃኒቶችን መርጨት እና ረጅም እጅጌ ያላቸውን ሸሚዞች እና ሱሪዎችን በመልበስ በሽታውን መከላከል ይቻላል።

በአመታዊ ጉባኤው በመገኘት የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ እንደተናገሩት፤ ኮሚቴው እያደረገ የሚገኘው ኢንቨስትመንት በሽታውን ከኢትዮጵያ ለማጥፋት የሚደረገውን ጥረት እያፋጠነ ይገኛል፡፡ ጤና ሚኒስቴር በሽታው በስፋት በሚገኝባቸው አካባቢዎች የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን በመጨመር የመከላከል እና አክሞ የማዳን ስራዎችን በስፋት እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡