Articles

የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ  የጄኤስአይ ዋና ስራ አስፈጻሚና ፕሬዝደንት ጋር ተወያዩ 

new

የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ  የጄኤስአይ ዋና ስራ አስፈጻሚና ፕሬዝደንት ማርጋሪት ክሮቲ  እና የጂኤስአይ ኢትዮጵያ ካንትሪ ዳይሬክተር ተደርገው አዲስ የተሾሙት ዶ/ር ቢኒያም ደስታ ጋር ተወያዩ ።


የጄኤስአይ ኢትዮጵያ ካንትሪ ዳይሬክተር መሰየሙ በጤና ሚኒስቴር እና ጄኤስአይ መሃል ያለውን ትብብር እና ግንኙነት እንደሚያጠናክር የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ በውይይታቸው የገለጹ ሲሆን፤ ጄኤስአይ የጤና ሚኒስቴር ጠንካራ አጋር መሆኑን እና ጤና ሚኒስቴር አጋርነቱን አጠናክሮ መቀጠል እንደሚፈልግ ገልጸዋል፡፡ 

32 ሀገራት እየተሳተፉ  ያሉበት የአፍሪካ መደበኛ ስፔሻላይዝድ የጤና፣ ስነ-ምግብ፣ ህዝብ እና መድሀኒት ቁጥጥር ውይይት በአፍሪካ ህብረት የስብሰባ አዳራሽ እየተካሄደ ነው

news

ውይይቱ “ጤናን ማዳበር በአፍሪካ፡ ሁለንተናዊ የጤና፣ የተመጣጠነ ምግብ፣ የህዝብ ቁጥር፣ የመድኃኒት ቁጥጥር፣ ወንጀል መከላከል እና ትምህርት ”በሚል መሪ ቃል የተካሄደ የሚገኝ ሲሆን ከአፍሪካ የልማት አጀንዳ ጋር በማጣጣም ከጤና፣ ከሥነ-ምግብ፣ ከሕዝብ እና ከመድኃኒት ቁጥጥር ጋር የተያያዙ በርካታ የሥራ ሰነዶችን ይጸድቃሉም ተብሎ ይጠበቃል።


በኮንፈረንሱ ከ32 አባላት የተውጣጡ ሚኒስትሮች እና ልዑካን ቡድኖች  የተገኙ ሲሆን ከተለያዩ የአፍሪካ ህብረት አካላት እና አጋር ድርጅቶች ተወካዮች የተውጣጡ  ኃላፊዎችና ባለሙያዎችም ተገኝተውበታል።


ከኢትዮጵያ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ እና የሚመለከታው ሌሎች የስራ ኃሌፊዎችና ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛል። 

ከ21 የምስራቅ እና ደቡብ አፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ የጤና እና የፋይናንስ አመራርና ባለሙያዎች የአድዋ ድል መታሰቢያን ጎበኙ

news

በጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ እና በሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ አስጎብኝነት በአድዋ ድል መታሰቢያ ተገኝተው የጎበኙት ከ21 የአፍሪካ አገራት የተውጣጡ የጤና እና የፋይናስ አመራርና ባለሙያዎች የጥቁር ህዝቦችን እውነተኛ ተጋድሎና የድል ብስራት ምን ይመስል እንደነበር የሚያመላክት የቅርስ ስብስቦች በአደዋ ድል መታሰቢያ ሙዝዚየም ተደራጅተው መቅረባቸው የኢትዮጵያን የእድገት ጉዞ በደምብ አሳይቶናል ብለዋል።

ለስብሰባ በኢትዮጵያ የተገኙት የUNFPA እና የአለም ጤና ድርጅት ጎብኚዎች የሰው ዘር መገኛ በሆነችው ኢትዮጵያ ተገኝተው ይሄንን የመሰለ ታሪካዊ ቦታ በመጎብኘታቸው ደስታቸውን በአድናቆት ገልፀዋል።

የአደዋ ድል መታሰቢያን ከጎበኙ በኃላ በሰጡት አስተያየት በአዲስ አበባ ከተማ እየመጣ ባለዉ ሁለንተናዊ ለዉጥ መደመማቸዉን ገልጸው ኢትዮጵያ ነጻነቷን አስከብራ ለጥቁር ህዝቦች የነጻነት ተምሳሌት እንደሆነች ሁሉ በልማቱም የአፍሪካ ምሳሌ መሆኗ የማይቀር መሆኑን ገልጸዋል።