በጤና ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ የተመራ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በቪየና ኦስትሪያ በተካሄደዉ 66ኛው የIAEA ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ተሳትፈዋል፡፡
"በኑክሌር መስክ ዓለም አቀፍ ትብብር!" በሚል መሪ ቃል በቪየና ኦስትሪያ በተካሄደዉ 66ኛው የIAEA ጠቅላላ ጉባኤ ላይ በጤና ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ የተመራ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን ተሳትፈዋል፡፡
በኤጀንሲው ዋና መስሪያ ቤት በቪየና ኢንተርናሽናል ሴንተር (VIC) በቪየና ኦስትሪያ የተካሄደዉ ይህ ጉባኤ ከኒዩክሌር ቴክኖሎጂ እና ሳይንስ ዙሪያ ለህክምና አገልግሎት ጥቅም የሚዉሉ ቴክኖሎጂዎችን በተለይም የካንሰር ጨረር ህክምናን ጨምሮ ለተለያዩ ህክምና ዘርፎች ጥቅም ላይ በሚዉሉ የኑክሌር ቴክኖሎጂ እና ሳይንስ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡
በ66ኛው የIAEA ጠቅላላ ጉባኤ የኢትዮጵያ ተወካዮች ከአክሽን ፎር ካንሰር ቴራፒ (PACT) መርሃ ግብሮች ቡድን ጋር በቀጥታ ውይይት በማድረግ በኢትዮጵያ እና በIAEA መካከል ስላለው እና የወደፊት የቴክኒክ ትብብር በተመለከተም ተወያይተዋል።