ሁለተኛው የአለም አቀፍ መድሃኒት አቅራቢዎች ኮንፍረንስ ተካሄደ
ኮንፍረንሱ የተካሄደው በኢትዮጵያ የሚታየውን የመድሃኒት አቅርቦት ውስንንት ለመሙላት እንዲቻል መድሃኒት አምራች እና አቅራቢዎችን ለመሳብ ታስቦ መሆኑን የኢትዮጵያ መድሃኒት አቅራቢዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አብዱልካዲር ገልገሎ ገልጸዋል፡፡
ዶ/ር አብዱልካዲር በንግግራቸው እንዳወሱት መድሃኒት አቅርቦት የባለድርሻ አካላት እና የካፒታል ስብጥር የሚጠይቅ በመሆኑ ከአቅራቢዎች ጋር ስትራተጂክ ፓርትነርሺፕ ግንኙነትን ማጠናከር እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።
መድሃኒት አቅርቦት በአለም አቀፍ ደረጃ ትኩረት የተሰጠው መሆኑን የተናገሩት የኢትዮጵያ ምግብ እና መድሃኒት ኤጀንሲ ዳይሬክተር ሄራን ገርባ ሲሆኑ፤ ኮቪድ 19 የመድሃኒት አቅርቦት ሰንሰለት ላይ ችግር መፍጠሩን ተናግረው ኤጀንሲያቸው የመድሃኒት ጥራት ቁጥጥር እና ደህንነት ላይ ትኩረት በማድረግ እየሰራ መሆኑን እና አገልግሎቱን ለማሻሻል የዲጂታላይዜሽን ስራ በመስራት ላይ መሆኑን ዳይሬክተሯ ተናግረዋል፡፡