ጳጉሜ 1 የበጎ ፈቃደኝነት ቀን አስመልክቶ የጤና ሚኒስቴር፣ የትምህርት ሚኒስቴር እና የስራና ክህሎት ሚኒስቴር በጋራ የሚያዘግጁት የሙሉ ቀን መርሃ ግብር በሚኒሊክ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ እና የመጀመርያ ደረጃ ትምህርት ቤት በተለያዩ ዝግጅቶች ተጀምሯል።
ዛሬ ጳጉሜ 1 የበጎ ፈቃደኝነት ቀን በማስመልከት በአራዳ ክፍለ ከተማ በሚኒሊክ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ እና የመጀመርያ ደረጃ ትምህርት ቤት የትምህርት ተቋማትን ፅዱና ውብ በማድረግ እንደዚሁም የተተከሉ ችግኞችን በማረም ፣ በመኮትኮት እና በመንከባከብ መርሃ ግብር ተጀምሯል።
በማስጀመሪያ መርሀ ግብሩ ላይ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ፣ የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌስር ብርሃኑ ነጋ እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸዉ እንግዶች ተገኝተዋል፡፡
መርሀ ግብሩ ለ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የትምህርት ተቋማት ለተማሪዎች ምቹ ፣ ፅዱ፣ ውብና ማራኪ እንዲሁም ሳቢ እንዲሆኑ እና ለመማር ማስተማሩ ሂደት ጉልህ ሚና እንዲኖራቸው ለማድረግ የሚያስችል ነው።
ጳጉሜ 1 የበጎ ፈቃደኝነት ቀን በተለያዩ መርሀ ግብሮች የሚቀጥል ይሆናል።