Articles

ሁለተኛው የአለም አቀፍ መድሃኒት አቅራቢዎች ኮንፍረንስ ተካሄደ 

group picture

ኮንፍረንሱ የተካሄደው በኢትዮጵያ የሚታየውን የመድሃኒት አቅርቦት ውስንንት ለመሙላት እንዲቻል መድሃኒት አምራች እና አቅራቢዎችን ለመሳብ ታስቦ መሆኑን የኢትዮጵያ መድሃኒት አቅራቢዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አብዱልካዲር ገልገሎ ገልጸዋል፡፡ 


ዶ/ር አብዱልካዲር በንግግራቸው እንዳወሱት መድሃኒት አቅርቦት የባለድርሻ አካላት እና የካፒታል ስብጥር የሚጠይቅ በመሆኑ ከአቅራቢዎች ጋር ስትራተጂክ ፓርትነርሺፕ ግንኙነትን ማጠናከር እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።


መድሃኒት አቅርቦት በአለም አቀፍ ደረጃ ትኩረት የተሰጠው መሆኑን የተናገሩት የኢትዮጵያ ምግብ እና መድሃኒት ኤጀንሲ ዳይሬክተር ሄራን ገርባ ሲሆኑ፤ ኮቪድ 19 የመድሃኒት አቅርቦት ሰንሰለት ላይ ችግር መፍጠሩን ተናግረው ኤጀንሲያቸው የመድሃኒት ጥራት ቁጥጥር እና ደህንነት ላይ ትኩረት በማድረግ እየሰራ መሆኑን እና አገልግሎቱን ለማሻሻል የዲጂታላይዜሽን ስራ በመስራት ላይ መሆኑን ዳይሬክተሯ ተናግረዋል፡፡ 

መድሃኒት የተላመደ የቲቢ በሽታ ከተስፋፋባቸው 33 ሀገራት ዝርዝር ውስጥ ኢትዮጵያ መውጣቷ መልካም አጋጣሚ ነዉ።

Dr. Lia Tadesse

ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ መድሃኒት የተላመደ የቲቢ በሽታን መግታት የድርጊት መርሃ ግብር ተቀብላ እየሰራች ነዉ ያሉት የጤና ሚኒስቴር ሚንስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ ናቸው፡፡ ክብርት ሚኒስትሯ ይህንን ያሉት በምስራቅ መካከለኛና ደቡብ አፍሪቃ (ECSA) ዓመታዊ የቲቢ በሽታ ምርመራ ላብራቶር የማጠናከሪያ ውይይት መድረክ ላይ ነዉ። በአገራችን በቲቢ መከላከል ዙሪያ የተሰሩ ስራዎች አበረታች ለውጥ እያሳዩ መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሯ በዋቢነትም በዓለም መድሃኒት የተላመደ የቲቢ በሽታ ከተስፋፋባቸው 33 ሀገራት ዝርዝር ውስጥ ኢትዮጵያ መውጣቷ መልካም አጋጣሚ እንደሆነ ገልጸዋል።


የECSA ዳይሬክተር ጀኔራል ፕ/ር ዮስዋ ደምብስያ እንደተናገሩት የአፍሪካ ችግሮች ለአፍሪካኖች እንዲፈቱ አስታውሰው በግሎባል ፈንድ የቲቢ ላብራቶር ምርመራ ማጠናከሪያ ኘሮጀክት ላለፉት ሰባት ዓመታት ሲያግዙ ለቆዩ ባለድርሻ አካላት ምስጋና አቅርበው ለወደፊትም ይህ ሥራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ድጋፋቸው እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል፡፡

ጳጉሜ 1 የበጎ ፈቃደኝነት ቀን አስመልክቶ የጤና ሚኒስቴር፣  የትምህርት ሚኒስቴር እና የስራና ክህሎት ሚኒስቴር በጋራ የሚያዘግጁት የሙሉ ቀን መርሃ ግብር በሚኒሊክ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ እና የመጀመርያ ደረጃ ትምህርት ቤት በተለያዩ ዝግጅቶች ተጀምሯል።

Dr. Lia Tadesse

ዛሬ ጳጉሜ 1 የበጎ ፈቃደኝነት ቀን በማስመልከት በአራዳ ክፍለ ከተማ በሚኒሊክ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ እና የመጀመርያ ደረጃ ትምህርት ቤት የትምህርት ተቋማትን ፅዱና ውብ በማድረግ እንደዚሁም የተተከሉ ችግኞችን በማረም ፣ በመኮትኮት እና በመንከባከብ መርሃ ግብር  ተጀምሯል።

በማስጀመሪያ መርሀ ግብሩ ላይ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ፣ የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌስር ብርሃኑ ነጋ እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸዉ እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

መርሀ ግብሩ ለ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የትምህርት ተቋማት ለተማሪዎች ምቹ ፣ ፅዱ፣ ውብና ማራኪ እንዲሁም ሳቢ እንዲሆኑ እና ለመማር ማስተማሩ ሂደት ጉልህ ሚና እንዲኖራቸው ለማድረግ የሚያስችል ነው።

ጳጉሜ 1 የበጎ ፈቃደኝነት ቀን በተለያዩ መርሀ ግብሮች የሚቀጥል ይሆናል።