Articles

የኢትዮጵያ የውስጥ ደዌ ህክምና ማህበር 7ኛው ዓመታዊ ሳይንሳዊ ጉባኤ ተካሄደ

group picture

በእለቱ በክብር እንግድነት የተገኙት የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር አየለ ተሾመ በጉባኤው መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር እንደገለጹት ባለፉት ሁለት አስርት አመታት የኢትዮጵያ ጤና ፖሊሲ በማህበረሰብ ጤና ማጎልበት፣ በሽታ መከላከልና የጤና አገልግሎት ሽፋን ማሻሻል ላይ ትኩረት አደርጎ የተሰራበት እና በዚህም ብዙ ስኬቶች  የተመዘገቡበት እንደነበር የተናገሩ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ግን የተላላፊ በሽታዎች ብቻ ሳይሆኑ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች እና አደጋዎችም በከፍተኛ ሁኔታ መጨመራቸውን ተከትሎ የከፍተኛ የፈውስ ህክምና ፍላጎትም እንዲሁ የጨመረበት ወቅት በመሆኑ የጤና ሚኒስቴር ለዚሁ ምላሽ በሁሉም የአገሪቱ ክፍሎች የሶስተኛ ደረጃ /tertiary care/  አገልግሎት ተደራሽነትንና ጥራትን ለማሻሻል እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ 

አባቶች፣ የቤተሰብ አባላትና ማህበረሰቡ ለሚያጠቡ እናቶች ትኩረት ሊሰጡ ይገባል

group picture

"ምቹ ሁኔታ ለሚያጠቡ እናቶች፣ እናስተምር፣ እንደግፍ!!" በሚል መሪ ቃል በአለም ለ30ኛ ጊዜ በሃገራችን ደግሞ ለ14ኛ ጊዜ የጡት ማጥባት ሳምንት እየተከበረ ሲሆን ዛሬ በደብረብርሃን ወይንሸት የተፈናቃዮች መጠለያ ከሚገኙ እናቶችና ህጻናት ጋር በአሉ ተከብሯል። 


በጤና ሚኒስቴር ሃገር አቀፍ የስርዓተ ምግብ ፕሮግራም አስተባባሪ የሆኑት ወ/ሮ ህይወት ዳርሰኔ በስነስርዓቱ ላይ እንደ ተናገሩት እናቶች ልጆቻቸውን እስከ ስድስት ወራት ጡት ብቻ ማጥባታቸው የህጻኑን ጤንነት ከመጠበቅና የተስተካከለ እድገት እንዲኖረው ከማስቻሉ ባለፈ ሃገራዊ ጥቅሙ ከፍተኛ ነው ብለዋል። እናቶች በማይመች ሁኔታ ውስጥም ቢሆኑ ለልጆቻቸው የጡት ወተትን መስጠት ማቋረጥ እንደሌለባቸው ለእናቶቹ አስገንዝበው አባቶች፣ የቤተሰብ አባላትና ማህበረሰቡም ለሚያጠቡ እናቶች ትኩረት ሊሰጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የኮሪያ መንግስት በኮፍ /KoFIH / ግብረሰናይ ድርጅት እና ኤክዚም ባንክ በኩል ለጤና ሚኒስቴር የኮቪድ 19 የዲያግኖስቲክ ላብራቶሪ ቁሳቁሶችን ድጋፍ አደረገ

The Korean government

በርክክብ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የተገኙ የጤና ሚኒስቴር  ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ የኮሪያ መንግሥት በተለያዩ ሥራዎች የጤና ሴክተሩን እንደሚያግዝ ተናግረው ይበልጥ በእናቶችና ህፃናት ጤና፣ በጤና መድህን አገልግሎት፣ የህክምና ባለሙያዎች ስልጠና፣ የህክምና ቁሳቁስ ጥገና እና ኮቪድ-19ን መከላከልና መቆጣጠር እንዲሁም የፅኑ ህሙማን ህክምና መሣሪያዎች ላይ ያደረጉትን ድጋፍ  አንስተዋል፡፡ 


የተደረገው ድጋፍ የኮቪድ-19ን ለመከላከልና ለመቆጣጠር  ጠቀሜታ  የጎላ  እንደሆነ ዶ/ር ሊያ ታደሰ  የተናገሩ ሲሆን ይህ ድጋፍ የሁለቱ ሃገራት ጥብቅ ግንኙነት ያሳያል ብለዋል፡፡


የኮፍ /KoFIH / ግብረ ሰናይ ድርጅት ፕሬዘዳንት ኘ/ር ቺያግ ዩፐ ኪም የኢትዮጵያ እና የደቡብ ኮሪያ ግንኙነት ረጅም አመታት ያስመዘገበ መሆኑን አውስተው የኮቪድ-19 የዲያግኖስቲክ ላብራቶሪ ቁሳቁሶችን ድጋፍ በተጨማሪ የመጀመሪያ ደረጃ ጤና ሥርዓት ማጠናከር ላይ በትኩረት  እንደሚሠሩ ተናግረዋል፡፡