Articles

ኦሀዮ ስቴት ዩኒቨርሲቲ ግሎባል ዋን ሄልዝ ፕሮግራም  በሰሜኑ ክፍል በነበረው ጦረነት ለተጎዱ የጤና ተቋማት ድጋፍ አደረገ

Ohio State University

በዛሬው እለት የተደረገው ድጋፍ 9 ሚሊዮን ብር የሚያወጡ የላብራቶሪ እቃዎች መሆናቸው ማወቅ የተቻለ ሲሆኑ ድጋፉ የተደረገው በአማራ እና በአፋር በክልል ለሚገኙ ስድስት ሆስፒታሎች ሲሆን በስድስቱ ሆስፒታሎች ውስጥ ላሉ የላብራቶሪ ክፍሎችን መልሶ ለማደረጃት የሚረዳ ድጋፍ ነው፡፡


በርክክብ ስነስርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ እንዳሉት በአገራቱ የነበረው ጦርነት የጤና ተቋማትን ማውደሙን ተከትሎ መልሶ ለማቋቋም በተደረገው ርብርብ ሁሉም ሆስፒታሎች ወደ ስራ እንዲገቡ መደረጉን አንስተዋል፡፡ ኦሀዮ ስቴት ዩኒቨርሲቲ ግሎባል ዋን  ሄልዝ ፕሮግራም ለዚህ ችግር ትኩረት በመስጠት  የሆስፒታሎችን ላብራቶሪዎች ሙሉ ለሙሉ ለመደገፍ መቻሉን ዶክተር ሊያ የተናገሩ ሲሆን በቴክኒክም የማጠናከር ስራ እየሰራ መሆኑንም ነው የገለጹት፡፡ 

የግሎባል ፈንድ አፈጻጸም እና ትግበራ በተመለከተ ከሲውዘርላንድ ከመጡ ከፍተኛ የተቋሙ አባላት ጋር ውይይት ተደረገ

Global Fund

ሲውዘርላንድ ጄኔቭ ከሚገኘዉ የግሎባል ፈንድ ዋና መስሪያቤት የመጣው ከፍተኛ የአመራርና የባለሙያዎች ቡድን ጋር በደተረገው ውይይት ላይ የሃይ ኢምፓክት አፍሪካ ሄድ ኦፍ ዲፓርትመንት እና የዴሊጌሽኑ መሪ የሆኑት ሊንደን ሞሪሰን እንዳሉት ኢትዮጵያ የተላያዩ ችግሮች ያጋጠሟት ቢሆንም በግሎባል ፈንድ ድጋፍ የሚደረግላቸዉ የጤና ፕሮግራሞች አፈጻጸም ግን ጥሩ በመሆኑ ደስተኞች መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡


በግሎባል ፈንድ ስር የሚከወኑ ፕሮግራሞችን እና የኮቪድ መከላከል ስራዎች መልካም ውጤት ያስገኙ መሆናቸው የገለጹት የጤና ሚኒስቴር ዶ/ር ሊያ ታደሰ ናቸው፡፡ የውጭ ምንዛሬ አለመረጋጋት እና ግጭት የግሎባል ፈንድ አፈጻፀም እና ትግበራ ላይ ያጋጠሙ ችግሮች እንደሆኑ ዶ/ር ሊያ ተናግረዋል፡፡ ያጋጠሙ የአቅርቦት ችግሮችን መቅረፍ ይገባል ያሉት ዶ/ር ሊያ፣ በግሎባል ፈንድ አፈጻጸም እና ትግበራ ላይ አጋር ድርጅቶች ያደረጉትን ተሳትፎ አድንቀዋል፡፡

በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የአቅመ ደካሞችን ቤት የማደስ ስራ ተጀመረ 

Dr. Lia Tadesse

የጤና ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማት በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የአቅመ ደካሞችን ቤት የማደስ ማስጀመሪያ መርኃ ግብር  ዛሬ በልደታ ክፍለ ከተማ፣ ወረዳ 5 የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ አስጀምረዋል።


መርኃ ግብሩ ላይ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ፣ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር አየለ ተሾመ እና የተጠሪ ተቋማት የስራ ኃላፊዎች እና ሌሎች የሥራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች ተገኝተዋል።


ጤና ሚኒስቴርና ከተጠሪ ተቋማት ጋር በመሆን በዘንድሮው መርሐግብር 12 አቅመ ደካሞችን በአዲስ አበባ እና 5 ቤቶችን በክልሎች የሚገነቡ ሲሆን ይህም የእርስ በእርስ የመደጋገፍ ባህልን የሚያዳብርና ለመጪው ትውልድም መልካም እሴትን የሚያሸጋግር ታላቅ በጎ ስራ ነው ብለዋል ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ፡፡