Articles

የግሎባል ፈንድ አፈጻጸም እና ትግበራ በተመለከተ ከሲውዘርላንድ ከመጡ ከፍተኛ የተቋሙ አባላት ጋር ውይይት ተደረገ

Global Fund

ሲውዘርላንድ ጄኔቭ ከሚገኘዉ የግሎባል ፈንድ ዋና መስሪያቤት የመጣው ከፍተኛ የአመራርና የባለሙያዎች ቡድን ጋር በደተረገው ውይይት ላይ የሃይ ኢምፓክት አፍሪካ ሄድ ኦፍ ዲፓርትመንት እና የዴሊጌሽኑ መሪ የሆኑት ሊንደን ሞሪሰን እንዳሉት ኢትዮጵያ የተላያዩ ችግሮች ያጋጠሟት ቢሆንም በግሎባል ፈንድ ድጋፍ የሚደረግላቸዉ የጤና ፕሮግራሞች አፈጻጸም ግን ጥሩ በመሆኑ ደስተኞች መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡


በግሎባል ፈንድ ስር የሚከወኑ ፕሮግራሞችን እና የኮቪድ መከላከል ስራዎች መልካም ውጤት ያስገኙ መሆናቸው የገለጹት የጤና ሚኒስቴር ዶ/ር ሊያ ታደሰ ናቸው፡፡ የውጭ ምንዛሬ አለመረጋጋት እና ግጭት የግሎባል ፈንድ አፈጻፀም እና ትግበራ ላይ ያጋጠሙ ችግሮች እንደሆኑ ዶ/ር ሊያ ተናግረዋል፡፡ ያጋጠሙ የአቅርቦት ችግሮችን መቅረፍ ይገባል ያሉት ዶ/ር ሊያ፣ በግሎባል ፈንድ አፈጻጸም እና ትግበራ ላይ አጋር ድርጅቶች ያደረጉትን ተሳትፎ አድንቀዋል፡፡

በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የአቅመ ደካሞችን ቤት የማደስ ስራ ተጀመረ 

Dr. Lia Tadesse

የጤና ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማት በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የአቅመ ደካሞችን ቤት የማደስ ማስጀመሪያ መርኃ ግብር  ዛሬ በልደታ ክፍለ ከተማ፣ ወረዳ 5 የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ አስጀምረዋል።


መርኃ ግብሩ ላይ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ፣ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር አየለ ተሾመ እና የተጠሪ ተቋማት የስራ ኃላፊዎች እና ሌሎች የሥራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች ተገኝተዋል።


ጤና ሚኒስቴርና ከተጠሪ ተቋማት ጋር በመሆን በዘንድሮው መርሐግብር 12 አቅመ ደካሞችን በአዲስ አበባ እና 5 ቤቶችን በክልሎች የሚገነቡ ሲሆን ይህም የእርስ በእርስ የመደጋገፍ ባህልን የሚያዳብርና ለመጪው ትውልድም መልካም እሴትን የሚያሸጋግር ታላቅ በጎ ስራ ነው ብለዋል ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ፡፡

ለትግራይ ክልል በአለም አቀፍ ድርጅቶች በኩል አስፈላጊ የህክምና መድሃኒቶችን የማድረሱ እንቅስቃሴ እንደቀጠለ ነው

 supplies

የኢትዮጵያ መንግስት ከሚሰራቸው ቀዳሚ ተግበራት መካከል የጤና አገልግትን ለሁሉም ዜጎች ማድረስ አንደኛው ሲሆን በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ህገ መንግስትም እያንዳንዱ ዜጋ የጤና አገልግሎት የማግኘት ጉዳይን በግልጽ ተጠቅሷል፡፡


ስለሆነም ዜጎች  የጤና አገልግሎት በፍትኃዊነት የማግኘት መብት ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችሉ የፖሊሲ አቅጣጫዎች በኢፊዲሪ የጤና ፖሊሲ ተካተዋል፡፡


ከዚህ አኳያ በአገራችን በተከሰቱ ግጭቶች ምክንያት ዜጎች የጤና አገልግሎቶችን የማግኘት ሰብዓዊና  ህገ መንግስታዊ መብቶች እንዳይስተጓጎሉ የኢትዮጵያ መንግስት በተለያዩ ጊዜያት ከአለም አቀፍ አጋር ድርጅቶች ጋር በመሆን ለጤና አገልግሎት አስላፈጊ የሆኑ ድጋፎችን የማድረስ ተግበራትን  አከናውኗል፣ እያከናወነም ይገኛል፡፡