Articles

100 የልብ ህሙማን ህጻናት ነጻ ህክምናና የአየር ትኬት ወጪ በመሸፈን በህንድ ሀገር ለማሳከም እንዲሁም በኢትዮጵያ የልብ ህሙማን ህጻናት መርጃ ማዕከል የሚሰጠዉን እገለገሎት በዘላቂነት ለማጠናከር ሁለት የመግባቢያ ሰነዶች ተፈረመ።

memorandums

የ100 የልብ ህሙማን ህጻናት ህክምናና የአየር ቲኬት ሙሉ ወጪ በመሸፈን ህንድ ሃገር ለማሳከም የመግባቢያ ሰነድ በጤና ሚኒስቴር፣ በኢትጵያ አየር መንገድ፣ በሮታሪ ኢንተርናሽናል እና በኢትጵያ ልብ ህሙማን ማህበር የተፈረመ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ የሚከሰቱ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን ለመከላከል የሚሰራውን ስራ የሚያጠናክር የመግባቢያ ሰነድ መሆኑን የጤና ሚኒስቴር ዶ/ር ሊያ ታደሰ አስታውቀዋል፡፡

በመንግስት ተቋማትና በኢትዮጵያ የልብ ህሙማን ህጻናት መርጃ ማእከል ብቻ ከ7,000 በላይ ህጻናት ለልብ ቀዶ ህክምና ወረፋ እየጠበቁ እንደሚገኙ የተናገሩት ዶ/ር ሊያ፤ እነዚህን ችግሮች ታሳቢ ባደረገ መልኩ ዛሬ ሁለት የመግባቢያ ሰነዱች እንደተፈረሙ ገልጸዋል፡፡

ጤንነቱ የተጠበቀ ማህበረሰብን መፍጠር ለሰላም መረጋገጥ የሚኖረው ድርሻ ከፍተኛ ነው።

75th Annual World Health Summit

የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ በስዊዘርላንድ ጀኔቫ "ሰላም ለጤና ጤና ለሰላም!” በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ባለው 75ኛው አመታዊ የአለም  ጤና ጉባኤ ላይ እንደተናገሩት ጤንነቱ የተጠበቀ ማህበረሰብን መፍጠር መቻል አስተማማኝና ዘለቄታዊ ያለው ሰላም እንዲኖር ከማድረግ አንጻር ያላው ድርሻ ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል።


ያለሰላም የተሟላ ጤናም መኖር አይችልም ያሉት ሚኒስትሯ  በሰሜን ኢትዮጵያ በተከሰተው ግጭት በርካታ የጤና ተቋማት እንደወደሙና እንደተዘረፉ በዚህም በርካታ ቁጥር ያለው ህብረተሰብ የተሟላ የጤና አገልግሎት እንዳያገኝ መስተጓጓሉን ጠቅሰው የኢትዮጵያ መንግስት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን የጤና አገልግሎትን ወደነበረበት ለመመለስ ከፍተኛ ጥረት እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

በጤና ሚኒስትር ክብርት ዶ/ር ሊያ ታደሰ የሚመራ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በ75 ኛው የአለም ጤና ጉባኤ ላይ እየተሳተፈ ነው።

World Health Assembly

የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ከተከሰተ ወዲህ በአካል የመጀመሪያ የሆነው ይህ የጤና ጉባኤ ግንቦት 14, 2014 ዓ.ም  በጄኔቫ ዝዊዘርላንድ በይፋ ተጀምሯል። 


"ሰላም ለጤና ጤና ለሰላም!"( "Peace for Health and Health for peace!") በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ያለው 75 ኛው የአለም ጤና ጉባኤ ላይ የአለማችን የማህበረሰብ ጤና  አሁናዊና ቀጣይ  ስትራቴጅክ ጉዳዮች ቀርበው ምክክርና ውይይት የሚደረግ ሲሆን ጉባኤው ለአንድ ሳምንት በጄኔቫ የሚቀጥል ይሆናል።