Articles

የጤና ሚኒስቴር ከቻይና መንግስት 10 ሚሊዮን ዶዝ የኮቪድ 19 ክትባት ተረከበ።

from the Chinese

የቻይና መንግስት ከዚህ ቀደም ለኢትዮጵያ ቃል ገብቶት ከነበረው የ20 ሚሊዮን ዶዝ የኮቪድ 19 ክትባት ውስጥ 10 ሚሊዮኑን የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ የቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ከሆኑት ዛኦ ዚያን እጅ በዛሬው እለት  ተረክበዋል፡፡ 


በርክክቡ ወቅት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ የቻይና መንግስት የኮቪድ 19 በሽታን ለመከላከል የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ እያደረገው ስላለው እገዛ ምስጋና አቅርበዋል። ለኢትዮጵያ ድጋፍ ከተደረገው 10 ሚሊዮን ውስጥ 5 ሚሊየን የሚሆነው በቻይና መንግስት ቀዳማዊት እመቤት የተበረከተ ሲሆን በአቻቸው የኢትዮጵያ ቀዳማዊት እመቤት ወ/ሮ ዝናሽ ታያቸው ስም ለጤና ሚኒስቴር የደረሰ መሆኑን የጠቀሱት ዶ/ር ሊያ ክትባቱም በዋነኝነት ተደራሽ የሚያደርገው ለእናቶች እና ለወጣቶች መሆኑንም አክለው ተናግረዋል፡፡ 

በመጀመሪያ ደረጃ ጤና ክብካቤ ፕሮጀክት ባለፉት ስድስት አመታት ከ58 ሚሊዮን በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት አግኝተዋል።

Dr. Lia Tadesse

የመጀመሪያ ደረጃ ጤና እንክብካቤ ፕሮጀክት በማስተባበር ፓዝፋይንደር ከአሜሪካ እና ከኮሪያ ህዝብና መንግስት በሚደረግለት ድጋፍ ባለፉት ስድስት አመታት በስድስት ክልሎችና በ451 ወረዳዎች ፕሮጀክቶችን ሲሰራ መቆየቱን ዶ/ር ሊያ ታደሰ የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ተናግረዋል፡፡

የጤና ሚኒስቴር ከዩኤስኤአይዲ ትራንስፎርም  ፕኤችሲዩ ጋር በመተባበር በመጀመሪያ ደረጃ ጤና እንክብካቤ በኦሮሚያ፣ በአማራ፣ በደቡብ፣ በሲዳማ፣ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ እና በትግራይ ክልል ጤና ቢሮዎችና አጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር ጥራት ያለው የስነ ተዋልዶ፣ የእናቶች፣ የጨቅላ ህፃናት፣ ታዳጊዎችና ወጣቶች እንዲሁም የስነ ምግብ አገልግሎቶች ተግባራዊ መደረጋቸው ዶ/ር ሊያ ታደሰ አንስተዋል፡፡

ዲጂታላይዝድ የታካሚዎች የጤና መረጃ አያያዝ መተግበሪያ ‹‹ዌልነስ ፓስ›› የሙከራ ትግበራ ስምምነት ተፈረመ

Welfare Pass

የጤና ሚኒስቴር መተግበሪያውን  ወደ ስራ ለማስገባት ከማስተር ካርድ፣ ከጋቪ እና ከጄ ኤስ አይ ጋር ዛሬ ስምምነት ተፈራርሟል። 


የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ በፊርማ ስነ ስርዓቱ ላይ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደተናገሩት ሚኒስቴር መስርያ ቤቱ በሁለተኛው የጤናው ዘርፍ እቅድ ውስጥ በመረጃ ላይ የተመሰረተ የውሳኔ  አሰጣጥ ስርዓት ለማጠናከር ጥራት ያለው መረጃ ማሰባሰብ፣ መተንተን እና መጠቀም ቁልፍ ተግባራት አድርጎ በልዩ ትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸው በዚሁ ወቅት ዲጅታል መተግበሪያው በሙከራ ደረጃ መጀመሩ በጤናው ዘርፍ ያለውን የመረጃ ስርዓት ለማዘመን እንደሚረዳ ገልፀዋል።


የታካሚዎችን የጤና መረጃ ስርዓት ፍሰትን ለማቀላጠፍ ማስተር ካርድ ‹‹ዌልነስ ፓስ›› የተባለው የዲጅታል መላ የሙከራ ትግበራውም በተመረጡ የጤና ተቋማት በ15 ወራት ውስጥ ለአንድ ሚሊዮን ተገልጋዮች ለማዳረስ የታለመ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡