Articles

የቦሩ ሜዳ ጠቅላላ ሆስፒታል በጦርነት ከደረሰበት ጉዳት አገግሞ ሁሉንም አገልግሎቶች በመስጠት ላይ ነው::

Boru Meda General Hospital

የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር አየለ ተሾመ የሆስፒታሉን የተለያዩ የስራ ክፍሎች ተዘዋውረው በጎበኙበት ወቅት እንደገለፁት ሆስፒታሉ ከደረሱበት ችግሮች ፈጥኖ በማገገም ለተገልጋዮች የተሟላ አገልግሎት መስጠት መጀመሩ የሚደነቅ ነው ብለዋል።


የቦሩ ሜዳ ጠቅላላ ሆስፒታል በጦርነቱ ወቅት ከፍተኛ ውድመት ከደረሰባቸው ሆስፒታሎች አንዱ እንደነበር ያስታወሱት ዶ/ር አየለ የተሟላ አገልግሎት እንዲሰጥ የተረባረቡትን ሁሉ አመስግነው በቀጣይም የጤና ሚኒስቴር የጎደሉ የህክምና መሳሪያዎችን ለማሟላት እየተፈፀሙ ያሉ ግዢዎችን በማፋጠን ሆስፒታሉ የሚጠናከርባቸውን አማራጮች ሁሉ እንደሚያመቻች ተናግረዋል።

የኮሪያ አለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (ኮይካ) ለጤና ሚኒስቴር የእናቶችና ጨቅላ ህጻናት ጤናን ለማሻሻል የሚረዳ የህክምና ቁሳቁሶችን ድጋፍ አደረገ::

Dr. Lia Tadesse

የኮሪያ አለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (ኮይካ) ለጤና ሚኒስቴር 31,076,584 ብር የሚያወጣ የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ ,በቤንሻንጉል ጉሙዝ እና አፋር ክልሎች የእናቶችና የጨቅላ ህጻናት ጤናን ለማሻሻል በዩኒሴፍ አመቻችነት የኮሪያ አለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (ኮይካ) ባደረገው  የገንዘብ ድጋፍ የህክምና መሳሪያዎች እና ለትራንስፖረት አገልግሎት የሚውሉ ሞተር ሳይክሎችን ለጤና ሚኒስትር አስረክቧል፡፡

የጤና ሚኒስቴር ከቻይና መንግስት 10 ሚሊዮን ዶዝ የኮቪድ 19 ክትባት ተረከበ።

from the Chinese

የቻይና መንግስት ከዚህ ቀደም ለኢትዮጵያ ቃል ገብቶት ከነበረው የ20 ሚሊዮን ዶዝ የኮቪድ 19 ክትባት ውስጥ 10 ሚሊዮኑን የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ የቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ከሆኑት ዛኦ ዚያን እጅ በዛሬው እለት  ተረክበዋል፡፡ 


በርክክቡ ወቅት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ የቻይና መንግስት የኮቪድ 19 በሽታን ለመከላከል የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ እያደረገው ስላለው እገዛ ምስጋና አቅርበዋል። ለኢትዮጵያ ድጋፍ ከተደረገው 10 ሚሊዮን ውስጥ 5 ሚሊየን የሚሆነው በቻይና መንግስት ቀዳማዊት እመቤት የተበረከተ ሲሆን በአቻቸው የኢትዮጵያ ቀዳማዊት እመቤት ወ/ሮ ዝናሽ ታያቸው ስም ለጤና ሚኒስቴር የደረሰ መሆኑን የጠቀሱት ዶ/ር ሊያ ክትባቱም በዋነኝነት ተደራሽ የሚያደርገው ለእናቶች እና ለወጣቶች መሆኑንም አክለው ተናግረዋል፡፡