የምግብ እጥረት ጠቋሚ በኢትዮጵያ ይፋ ይተደረገው ‹‹ግጭት ባለባቸው ቦታዎች የምግብ አቅርቦትን ለማሻሻል በአጋርነት መሥራት›› በሚል መሪ ቃል ነው፡፡
የምግብ እጥት ብዙ ችግሮችን የሚያካትት በመሆኑ በትኩረት መሰራት እንዳለበት የጠቆሙት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ፤ በ2021 የነበረውን ሂደት በሚያስረዳው ሪፖርት የመክፈቻ ዝግጅት ላይ ባደረጉት ንግግር እንደተናገሩት የኢትዮጵያ መንግስት የምግብና ስነ-ምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተለያዩ ፖሊሲዎችንና ስትራቴጂዎችን በመተግበር ላይ ይገኛል።
የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ለመከላከልና ለመቆጣጠር ተሻሽሎ የወጣው መመሪያ ቁጥር 882/2014 በተመለከተ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰተዋል፡፡
ባለፉት ሁለት አመታት በሃገራችን ኢትዮጵያ ወረርሽኙን ለመቆጣጠር እና ለመግታት የተለያዩ መመሪያዎችንና ደንቦችን በማውጣት ተግባራዊ ሲደረግ ቆይቷል፡፡