Articles

‘የጤና መረጃ ሥርዓትን ለማሻሻል አጋርነት እና ትብብርን ማጠናከር’ በሚል መሪ ቃል በሀገር አቀፍ ደረጃ የጤና መረጃ ሳምንት ለመጀመሪያ ጊዜ እየተከበረ ነው።

DATA WEEK

በበዓሉ መክፈቻ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት በጤና ሚኒስቴር የሚኒስትር ፅ/ቤት ሀላፊ ዶ/ር ሩት ንጋቱ በጤናው ሴክቴር የሚታየውን የመረጃ ጥራት ተደራሽነት እና አጠቃቀም ጉድለት በመቅረፍ የጤና አግልግሎት ዘርፉን ማሻሻል እና ተደራሽ ማድረግ ዋና የትኩረት አቅጣጫው መሆኑንን ገልፀው የጤናው ዘርፍ የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ የትግበራ ዘመን የጤና መረጃ ጥራትን ለማሻሻል የመረጃ አጠቃቀም ባህሪን ለማጎልበት እና መረጃን ዋቢ ያደረገ የውሳኔ አስጣጥ አስራርን ለማስረፅ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የንግስት እሌኒ መሀመድ መታሰቢያ ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የተለያዩ  አገልግሎቶች ማስጀመሪያ ፕሮግራም ተካሄደ

Inauguration

በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ እንደተናገሩት ጥራት ያለው ህክምና ተደራሽነትን ለማሻሻልና  የስፔሻሊቲ እና ሰብ ስፔሻሊቲ ህክምና አገልግሎትን ለመስጠት የተለያዬ የህክምና ቴክኖሎጅዎችን መጠቀም እንደሚያስፈልግ ገልፀው በዛሬው እለትም በዋቻሞ ዩንቨርስቲ የንግስት እሌኒ መሀመድ መታሰቢያ ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከ40 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ ተደርጎበት የተተከለ የሲቲ ስካን ማሽን መርቀው ስራ አስጀምረዋል።


በተጨማሪም በሆስፒታሉ ለሚገነቡት የኦክስጅን ማምረቻና 450 አልጋ የሚይዝ የእናቶችና ህፃናት ጤና አገልግሎት መስጫ ማዕከል የመሰረተ ድንጋይ አስቀምጠዋል።


የዋና ዋና ከተሞች የድንገተኛ፤ አደጋና ጽኑ ህክምና አገልገሎት ማሻሻያ ፕሮግራም (Major city Emergency and Critical services Improvement Program(MECIP) በተመለከተም የቅድመ ጤና ተቋም የጥሪ ማዕከል አገልግሎትን አስጀምረዋል።

ኢትዮጵያ ከ20 ሚሊዮን በላይ ዜጎቿን የኮቪድ-19 በሽታ መከላከያ ክትባት እንዲከተቡ አድርጋለች!

Dr. Tegene Regassa

የ2ኛ ዙር የኮቪድ-19 ክትባት ዘመቻ አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫውን የሰጡት የጤና ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነትና ኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር ዶ/ር ተገኔ ረጋሳ ሁለተኛ ዙር የኮቪድ 19 ክትባት ዘመቻ በአገር አቀፍ ደረጃ ከየካቲት 7 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ እየተሰጠ እንደሚገኝ የገለጹ ሲሆን በአሁኑ ዘመቻ የተሰጠውን ከ14 ሚሊዮን በላይ ክትባትን ጨምሮ በአጠቃላይ ከ20 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን መከተብ መቻሉን አስታውቀዋል፡፡


እንደ ዳይሬክተሩ ገለጻ ከሆነ 17 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ሙሉ ለሙሉ ክትባት የወሰዱ ሲሆን ከአንድ መቶ ዘጠና ሁለት ሺህ በላይ የሚሆኑት የማጠናከርያ ክትባቱን (Booster dose) ተከትበዋል፡፡ በጥቅሉ ከ25 ሚሊዮን በላይ ክትባት ጥቅም ላይ እንዲውልም ተደርጓል፡፡  


በዘመቻውም በመጀመርያው ዙር የመከላከያ ክትባቱ ያልተሰጠባቸው የአማራ እና የአፋር ክልሎችን በማካተት ክትባቱን መስጠት መቻሉንም ዳይሬክተሩ አክለው ገልጸዋል፡፡