‘የጤና መረጃ ሥርዓትን ለማሻሻል አጋርነት እና ትብብርን ማጠናከር’ በሚል መሪ ቃል በሀገር አቀፍ ደረጃ የጤና መረጃ ሳምንት ለመጀመሪያ ጊዜ እየተከበረ ነው።
በበዓሉ መክፈቻ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት በጤና ሚኒስቴር የሚኒስትር ፅ/ቤት ሀላፊ ዶ/ር ሩት ንጋቱ በጤናው ሴክቴር የሚታየውን የመረጃ ጥራት ተደራሽነት እና አጠቃቀም ጉድለት በመቅረፍ የጤና አግልግሎት ዘርፉን ማሻሻል እና ተደራሽ ማድረግ ዋና የትኩረት አቅጣጫው መሆኑንን ገልፀው የጤናው ዘርፍ የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ የትግበራ ዘመን የጤና መረጃ ጥራትን ለማሻሻል የመረጃ አጠቃቀም ባህሪን ለማጎልበት እና መረጃን ዋቢ ያደረገ የውሳኔ አስጣጥ አስራርን ለማስረፅ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ መሆኑን ተናግረዋል፡፡