Articles

በፌደራል ጤና ሚኒስቴር እና ግብርና ሚኒስቴር የሚመራ የዓለም ጤና ድርጅት የምግብና የእርሻ ድርጅትን ያካተተ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ቡድን በድርቅ የተጎዳዉን የሱማሌ ክልል ሸበሌ ዞንን ጎብኝቷል።

Somali

የጎዴ አጠቃላይ ሆስፒታል የምግብ እጥረት ህክምና መስጫ ማዕከልን፣ ፈጣን ምላሽ ህክምና አሰጣጥን እንዲሁም በጎዴ ወረዳ የክትባት፣ የስነ ምግብ፣ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት ድጋፍ፣ የእንስሳት ምገባ ድጋፍ አገልግሎት ለማህበረሰቡ በፌደራል በክልልና በአጋር ድርጅቶች ቅንጅት እየተሰጠ የሚገኝበትን ሁኔታም ተመልክቷል።


ከጉብኝቱ በተጨማሪም ቡድኑ ከክልሉ ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ሙስጤፌ መሃመድ እና ከሌሎች የክልሉ ሃላፊዎች ጋር በድርቅ የተጎዱ ቦታዎችን ምላሽ አሰጣጥና ድጋፍ ዙሪያ ውይይት አድርጓል። 

በኢትዮጵያ ሁለተኛ የሆነው የካንሰር ህክምና ጨረር አገልግሎት መስጫ ማዕከል ተመረቀ

Inauguration

በኢትዮጵያ በየአመቱ ከሰባ ሺ በላይ ዜጎች በተለያየ አይነት የካንሰር በሽታዎች እንደሚጠቁ ጥናቶች ያሳያሉ፡፡ ለእነዚህ የማህበረሰብ ክፍሎች የጨረር ህክምና አገልግሎት ሲሰጥ የቆየው የጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ብቻ ነበር፡፡


በዛሬው ዕለት የተመረቀውና አገልግሎት እየሰጠ የሚገኘው የጅማ ዩንቨርስቲ ሆስፒታል የጨረር ህክምና ማዕከል በከፍተኛ ወጪ መዘጋጀቱና አገልግሎት መጀመሩ በጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ላይ ብቻ ተወስኖ የቆየው የጨረር ህክምና አገልግሎት ጫናን በመቀነስ በህክምናው ተደራሽነት ላይ ትልቅ አስተዋጽኦ ያደርጋል ተብሏል፡፡

ሰማሪታንስ ፐርስ ኢንተርናሽናል ሪልፍ የእርዳታ ድርጅት ለኢትዮጵያ 12.5 ሚሊዮን ብር የሚገመት የህክምና ቁሳቁስና ግብአት ድጋፍ አደረገ

Samaritan’s Purse

የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ በቦሌ አየር ማረፊያ ተገኝተው ከሰማሪታንስ ፐርስ ኢንተርናሽናል ሪልፍ ካንትሪ ዳይሬክተር ሪል ላን ድጋፉን ተረክበዋል፡፡ ዶ/ር ሊያ በርክክብ ስነስርዓቱ ጊዜ እንደተናገሩት መቀመጫውን በአሜሪካ አገር ያደረገው የሰማሪታንስ ፐርስ ኢንተርናሽናል ሪልፍ በኢትዮጵያ ከንጹህ የመጠጥ ውኃ አቅርቦትና ሳኒቴሽን፣ ከኮቪድ-19 እና በሌሎች የድንገተኛ ምላሽ ድጋፍ ስራዎችን ሲሰራ የቆየ ተቋም መሆኑን አንስተው አሁን 12.5 ሚሊዮን ብር የሚያወጡ የህክምና ግብአትና መሳሪያዎች ድጋፍ ማድረጉን ገልጸዋል፡፡