በፌደራል ጤና ሚኒስቴር እና ግብርና ሚኒስቴር የሚመራ የዓለም ጤና ድርጅት የምግብና የእርሻ ድርጅትን ያካተተ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ቡድን በድርቅ የተጎዳዉን የሱማሌ ክልል ሸበሌ ዞንን ጎብኝቷል።
የጎዴ አጠቃላይ ሆስፒታል የምግብ እጥረት ህክምና መስጫ ማዕከልን፣ ፈጣን ምላሽ ህክምና አሰጣጥን እንዲሁም በጎዴ ወረዳ የክትባት፣ የስነ ምግብ፣ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት ድጋፍ፣ የእንስሳት ምገባ ድጋፍ አገልግሎት ለማህበረሰቡ በፌደራል በክልልና በአጋር ድርጅቶች ቅንጅት እየተሰጠ የሚገኝበትን ሁኔታም ተመልክቷል።
ከጉብኝቱ በተጨማሪም ቡድኑ ከክልሉ ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ሙስጤፌ መሃመድ እና ከሌሎች የክልሉ ሃላፊዎች ጋር በድርቅ የተጎዱ ቦታዎችን ምላሽ አሰጣጥና ድጋፍ ዙሪያ ውይይት አድርጓል።