"የእናቶችን ሞት ለማስቀረት ሁሉም አካላት ቀዳሚ አጀንዳ በማድረግ ሊሰሩ ይገባል!" ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ
"በማንኛውም ሁኔታ ከወሊድ በሁዋላ በደም መፍሰስ ምክንያት የሚከሰተውን የእናቶች ሞት እጅ ለእጅ ተያይዘን እንግታ" በሚል መሪ ቃለ በአማራ ክልላዊ መንግስት ደሴ ከተማ በተከበረበት ወቅት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ እንደተናገሩት በሀገራችን በቀን ከሰላሳ በላይ እናቶች ከወሊድ ጋር በተያያዘ ህይወታቸውን እንደሚያጡ ተናግረው እንደ ደሴ ባሉ በህውሀት አሸባሪ ቡድን የጦርነት ጥቃት እና ዘረፋ በተከሰተባቸው አካባቢዎች ችግሩ ሊከፋ እንደሚችል በመረዳት ሁሉም አካላት በከፍተኛ ትኩረት ሊሰሩ እንደሚገባ አስረድተዋል፡፡
አሸባሪው ብድን የጤና ተቋማቱን ቢያወድሙና ቢዘርፉም ጠንካራ መንፈሳችንን ግን ሊነኩት አይቻላቸውምና ደግመን ተረባርበን በመገንባት ለእናቶችና ለሌሎችም የጤና አገልግሎቶችን በተሻለ እናቀርባለን ብለዋል፡፡