Articles

በጅግጅጋ ከተማ በተካሄደው 23ኛ የጤናው ዘርፍ ጉባኤ ተሳታፊ የነበሩ ሁሉም ታዳሚዎች የኮቪድ 19 ምርመራ እንደተደረገላቸው ተገለጸ።

RDT test

ይህም በርካታ ቁጥር ያለው ተሳታፊ ለሚገኝባቸው ወሳኝ  ሀገራዊ ሁነቶች  ምሳሌ የሚሆን ተግባር መሆኑ ተነግሯል። 
"ፈጣን ምላሽ ሰጪ የጤና ስርአት በአዲስ ምእራፍ" በሚል መሪ ቃል  የሱማሌ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት መዲና በሆነችው ጅግጅጋ  ሲካሄድ የሰነበተው የጤናው ዘርፍ ጉባኤ ሁሉም ተሳታፊዎች ከጉባኤው  አንድ ቀን አስቀድሞ የኮቪድ 19 ምርመራ የወሰዱበትና ከቫይረሱ ነጻ መሆናቸው የተረጋገጠ ተሳታፊዎች የተገኙበት እንዲሁም ሌሎችም  ሁሉም የጥንቃቄ መንገዶች የተተገበሩበት እንደሆነ ገልጸው  ለሌሎች ተመሳሳይ ሀገራዊ ሁነቶች ትምህርት የሰጠ እንደነበር ተሳታፊዎች ተናግረዋል። 

የጤና ሚኒስቴር በአዲስ መልክ ያበለፀገውን ዌብ ሳይት ይፋ አደረገ

website

አዲሱ ዌብ ሳይት ሁለገብና መረጃዎችን በተደራጀና ሳቢ በሆነ መንገድ ለተጠቃሚዎችና ለባለድርሻ አካላት የሚያደርስ መሆኑን የገለፁት ዌብ ሳይቱ እውን መሆኑን ያስተዋወቁት በጤና ሚኒስቴር የሚኒስትሯ ከፍተኛ አማካሪ ዶ/ር ዳንዔል ገብረሚካኤል ናቸው።


የቀድሞው ዌብ ሳይት መረጃ እንደልብ የማይገኝበትና ሳቢ እንዳልነበረ ቅሬታ የሚቀርብበት ነበር ያሉት ዶ/ር ዳንዔል አዲሱ ዌብ ሳይት በተገቢ መረጃዎች የተደራጀና ለአጠቃቀም ሳቢ እና ቀላል ሆኖ የቀረበ ሲሆን ማንኛውም  ከሀገር ዉጪም ሆነ በሀገር ውስጥ ለሚገኙ ተገልጋዮች የኢ ላይብረሪ ፣ኦን ላይን የበጎ ፈቃድና ልገሳ አገልግሎት፣ የአስተያየት/ቅሬታ ማቅረቢያ፣ የቴሌቪዥን ቻናል፣ የዲጂታል ጤና ሲስተሞች፡ የጤና ማህበራት የጥናትና ምርምር ውጤቶችን እና ሌሎችንም ያካተተ መሆኑ ተገለጿል።

በጅግጅጋ ከተማ የተካሄደው 23ኛው የጤና ዘርፍ ጉባኤ የ2014 ዓ.ም ዕቅድን በጋራ ለማሳካት የሚያስችል የቃል ኪዳን ስምምነት ከክልሎችና ከተማ መስተዳድሮች ጋር በመፈራረም ተጠናቋል

final

"ምላሽ ሰጪ የጤና ስርዓት በአዲስ ምዕራፍ " በሚል መሪ ቃል ለሶስት ቀናት በጅግጅጋ ከተማ ሲከናወን የቆየው 23ኛው የጤናው ዘርፍ ዓመታዊ ጉባዔ ተጠናቋል።


በጉባኤው ማጠናቀቂያ ላይ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ ከዘጠኝ የክልልና ሁለት የከተማ መስተዳድር የጤና ቢሮ ኃላፊዎች ጋር ባደረጉት ስምምነት መሠረት በበጀት ዓመቱ የተቀመጡ ዕቅዶችን በጋራ ለማሳካት የሚያስችሉ ግብዓቶችን በማሟላትና የተቀናጀ ርብርብ በማድረግ ለህብረተሰቡ ተገቢውንና ጥራት ያለውን የጤና አገልግሎትፍትሃዊና ተገልጋይ ተኮር በሆነ መልኩ ለማቅረብ በስምምነት ፊርማቸው በጋራ ቃል ገብተዋል።


ጉባዔውን በንግግር የዘጉት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ ጉባኤው በተሳካ ሁኔታ እንዲከናወን ያደረጉትን አጋር አከላት እና በተለይም የሶማሌ ክልልን ካመሰገኑ በኋላ ሁላችንም በያለንበት ለህብረተሰቡ ሁሉን አቀፍ የጤና አገልግሎት ለማዳረስ ተግተን መስራት ይገባናል ብለዋል።