Articles

ፖሊዮን ጨርሶ ለማጥፋት የሚያስችል የክትባት ዘመቻ  በይፋ ተጀመረ

Dr. Dereje Duguma

ከፖሊዮ ነጻ የሆነ አለም እንፍጠር በሚል መሪ ቃል በአገር አቀፍ ደረጃ በሲዳማ ክልል በአዋሳ ከተማ እና በደቡብ ክልል ጌዲዮ ዞን ዲላ ከተማ የክትባት ዘመቻ መርሀግብር ያስጀመሩት የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ  በመርሀግብሩ እንደተናገሩት የጤና ሚኒስቴር ፖሊዮን ለማጥፋት በመደበኛ ክትባትና በዘመቻ በሚሰጥ ክትባት ከሀገራችን  ለማጥፋት ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው።


ባለፉት አመታትም በተከናወነው ስራ ፖሊዮን ማጥፋት ተችሎ የነበረ ሲሆን በአሁኑ ወቅት  በተለያዩ አከባቢዎች  እየታየ ያለውን የልጅነት ልምሻ በሽታ ለማጥፋትም እስከ ጤና ኬላ በተዘረጋ መዋቅር እና ከአጋር አካላት ጋር በተቀናጀ አሰራር እየተተገበረ መሆኑን ተናግረው  ይህም መንግስት ለሕጻናት ጤና መሻሻል ትልቅ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ ማሳያ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ 

በጤናው ዘርፍ የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት የሰጡ የአዲስ አበባ ወጣቶች እውቅና ተሰጣቸው

youth

የጤና ሚኒስቴር ከአዲስ አበባ ወጣቶች በጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ቢሮ ጋር በመተባበር በጤናው ዘርፍ የክረምት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት የእውቅና አሰጣጥ መርሃ ግብር በዛሬው እለት አካሂዷል፡፡ 


እውቅናውን  የተሰጣቸው የአዲስ አበባ ወጣቶች ሲሆኑ በቅዱስ አማኑኤል የአዕምሮ ስፔሻላይዝድ  ሆስፒታል፣ በአለርት ማእከል፣ በቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል፣ በጥሩነሽ ቤልጂንግ  ሆስፒታል፣ በካቲት 12 ሜዲካል ኮሌጅ፣ በራስ ደስታ ሆስፒታል እና በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒዬም ሜዲካል ኮሌጅ ወስጥ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሲሰጡ የቆዩ ወጣቶች ናቸው፡፡


የእውቅና አሰጣጥ መድረኩን በንግግር የከፈቱት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር አየለ ተሾመ እንደ ጤና ሴክትር ብዙ ነገሮችን በገንዘብ እጥረት ምክንያት ማሳካት በማንችልበት አገር ውስጥ የበጎ ፈቃደኝነት አገልግሎት  መሰረታዊ ጉዳይ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡

በአሜሪካ መንግስት 453,600 ዶዝ ጆንሰን ጆንሰን ኮቪድ19 ክትባቶች ለኢትዮጵያ ድጋፍ ተደረገ 

donation


ከአሜሪካ መንግስት ዓለም አቀፍ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ስርጭትን ለመከላከል 453,600 ዶዝ ጆንሰን ጆንሰን ኮቪድ19 ክትባቶች ለኢትዮጵያ ድጋፍ ተደረገ ፡፡


በርክክቡ ስነ ስርዓት ላይ የተገኙት የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሰሐረላ አብዱላሒ ባደረጉት ንግግር ከአሜሪካ መንግስት ወደ ኢትዮጵያ የገባው ክትባት ለአራተኛ ዙር እንደሆነ እና በዛሬው እለትም 453,600 ዶዝ ጆንሰን ጆንሰን ኮቪድ19 ክትባቶችን መረከባቸውን እንዲሁም በቀጣይ ተጨማሪ 504 ሺ ክትባቶች እንደሚገቡ ይፋ አድርገውዋል፡፡