"የጤና መድህን አባላትን ቁጥር በማሳደግ የዜጎችን ተጠቃሚነት የማረጋገጡ ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል" የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሠ
አገር አቀፍ የጤና መድህን አገልግሎት የ2013 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና የ2014 ዓ.ም ዕቅድ ግምገማ ጉባኤ ማጠቃለያ ላይ ተገኝተው የስራ አቅጣጫ የሰጡት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሠ እንደተናገሩት የጤና መድህን አባላትን ቁጥር በማሳደግ የዜጎችን ተጠቃሚነት የማረጋገጡ ስራ በ2014 በጀት ዓመትም ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
የጤና መድህን አባላትን ቁጥር በማሳደግና ዘላቂነት ያለው የፋይናንስ ስርዓትን በመፍጠር በጤና ተቋማት ላይ የሚነሱ ችግሮችን ለመቅረፍ እንደሚረዳ የገለጹት ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሠ ይህንን ለማሳካትም ከላይ እስከታች ያለው የጤና መዋቅር አመራር በመደጋገፍና በቅንጅት መንፈስ ሊሰራ ይገባልም ብለዋል፡፡