Articles

በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የጥፋት ቡድኑ ባደረሰው ጉዳት ተፈናቅለው ባህርዳር ለሚገኙ ወገኖችና በክልሉ ውስጥ  ጉዳት ለደረሰባቸው  15 ጤና ጣቢያዎች  ድጋፍ ተደረገ 

Amhara

በጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴአታ ወ/ሮ ሠሐረላ አብዱላሂ የተመራ ከጤና ሚኒስቴር፤ ፌዴራል ሆስፒታሎችና ከተጠሪ ተቋማትና ከግሉ ዘርፍ የተውጣጣ ቡድን በአማራ ክልል በባህርዳር ከተማ በህውሃት የጥፋት ቡድን ባደረሰባቸው ጉዳት ተፈናቅለው ጉዳት የደረሰባቸው ዜጎችን ጎብኝቷል።

 
ቡድኑ ከደሴና ኮምቦልቻ አከባቢ በፀጥታው ችግር ምክንያት ተፋናቅለው በባህርዳር ከተማ በዘንዘልማ የተፈናቃዮች መጠለያ የሚገኙትን የጎበኙ ሲሆን በከተማው አስራ አራት ሺ አምስት መቶ ሃያ ሁለት ሺህ የሚሆኑ ተፈናቃይ ወገኖች እንደሚገኙና በመጠለያ ቦታው አራት ሺ ሁለት መቶ ሃምሳ ሁለት ተፈናቃዮች የሚገኙ መሆኑ ታውቋል፡፡ ለተፈናቀሉ ወገኖች የጤና አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ የክልሉ ጤና ቢሮ ባለሙያዎችን መድቦ ክሊኒክ የከፈተላቸው ሲሆን ከተፈናቀሉ የጤና ባለሙያዎች እና አጋር ድርጅቶች ጋር በመቀናጀት የህክምና አገልግሎትና የማልኑትሪሽን ችግር ልየታ ስራ እየተሰራ መሆኑን መመልከት ተችለዋል። 

የጡት ካንሰር ግንዛቤ ወር የክብርት ፕሬዚደንት መልዕክት

HE the President

የጥቅምት ወር የጡት ካንሰር ግንዛቤ ወር ነው። የጡት ካንሰር ሴቶችን በከፍተኛ  ደረጃ ያጠቃል። በአገራችን ታካሚዎች ወደ ጤና ተቋም የሚሄዱት ዘግይተው ነው። የሚታዩ ምልክቶችን በጊዜ ለመለየት ቅድመ ምርመራ እንዲደረግ የሚመለከታቸው ሁሉ በቂ ግንዛቤ ሊይዙ ይገባል። ይህ ባለመሆኑ ብዙዎችን አጥተናል።


ከአገራችን የተለያዩ ክፍሎች ለጨረርና ለኪሞ ሕክምና የሚመጡ ሴት ወገኖቻችን መጠለያ ቦታ ስለሌላቸው ለተጨማሪ ችግር ይጋለጣሉ። ችግሩን ለመቅረፍ ለእነዚህ ሕሙማን ማረፍያ ቦታ በማዘገጀት፣  ወደ ሆስፒታል በማመላለስ፣ መድሃኒት ግዢ ላይ በመደገፍ ወዘተ . . . ከሚሠሩ ድርጅቶች መካከል "ፒንክ ሃውዝ" የተባለውን በቅርብ ጎብኝቻለሁ። ይህንንና ተመሳሳይ ተቋሟችን በመደገፍ ሴቶች በጊዜ ከተደረሰበት ሊታከም በሚችል በሽታ እንዳይጎዱ እናድርግ።

"የጤና መድህን አባላትን ቁጥር በማሳደግ የዜጎችን ተጠቃሚነት የማረጋገጡ ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል" የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሠ

lia

አገር አቀፍ የጤና መድህን አገልግሎት የ2013 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና የ2014 ዓ.ም ዕቅድ ግምገማ ጉባኤ ማጠቃለያ ላይ ተገኝተው የስራ አቅጣጫ የሰጡት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሠ እንደተናገሩት የጤና መድህን አባላትን ቁጥር በማሳደግ የዜጎችን ተጠቃሚነት የማረጋገጡ ስራ በ2014 በጀት ዓመትም ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡


የጤና መድህን አባላትን ቁጥር በማሳደግና ዘላቂነት ያለው የፋይናንስ ስርዓትን በመፍጠር በጤና ተቋማት ላይ የሚነሱ ችግሮችን ለመቅረፍ እንደሚረዳ የገለጹት ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሠ ይህንን ለማሳካትም ከላይ እስከታች ያለው የጤና መዋቅር አመራር በመደጋገፍና በቅንጅት መንፈስ ሊሰራ ይገባልም ብለዋል፡፡