አዳዲስ ምሩቃን ሃኪሞችን ወጪን በመጋራት ወደ ስራ ለማስገባት ከጥቂት ሳምንታት በፊት ይፋ የተደረገውን ፕሮጀክት አስመልክቶ ምክክር ተደርገ
ጤና ተቋማት ያለባቸውን የሰው ሃይል እጥረት ለማቃለል እና ለተመራቂ ሃኪሞች የስራ እድል ለመፍጠር ይፋ የተደረገውን የ3 ዓመት ፕሮጀክት ስራ በተመለከተ ወርክሾፕ ተካሂደዋል።
ጤና ሚኒስቴር ከአጋር ድርጅቶች እና ክልል ጤና ቢሮዎች ጋር በመሆን ወጪን በመጋራት አዳዲስ ሃኪሞችን ወደ ስራ ለማስገባት በተጀመረው ፕሮጀክት መሰረት እየሰራ መሆኑን የተናገሩት በጤና ሚኒስቴር የሰው ሀብት አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ ሀብታሙ ደምሴ በፕሮጀክቱ ከ2011 ጀምሮ ተመርቀው ያልተቀጠሩ 2898 ሃኪሞችን ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችል የበጀት ዝግጅት መጠናቀቁን ገልጸዋል፡፡