Articles

አዳዲስ ምሩቃን ሃኪሞችን ወጪን በመጋራት  ወደ ስራ ለማስገባት ከጥቂት ሳምንታት በፊት ይፋ የተደረገውን ፕሮጀክት አስመልክቶ ምክክር ተደርገ

HR

ጤና ተቋማት ያለባቸውን የሰው ሃይል እጥረት ለማቃለል እና ለተመራቂ ሃኪሞች የስራ እድል ለመፍጠር ይፋ የተደረገውን የ3 ዓመት ፕሮጀክት ስራ በተመለከተ ወርክሾፕ ተካሂደዋል።


ጤና ሚኒስቴር ከአጋር ድርጅቶች እና ክልል ጤና ቢሮዎች ጋር በመሆን ወጪን  በመጋራት አዳዲስ ሃኪሞችን ወደ ስራ ለማስገባት በተጀመረው ፕሮጀክት መሰረት እየሰራ መሆኑን የተናገሩት በጤና ሚኒስቴር የሰው ሀብት አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ ሀብታሙ ደምሴ በፕሮጀክቱ ከ2011 ጀምሮ ተመርቀው ያልተቀጠሩ 2898 ሃኪሞችን ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችል የበጀት ዝግጅት መጠናቀቁን ገልጸዋል፡፡

ትኩረት የሚሹ የሀሩራማ በሽታዎችን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር ሁሉም ባለድርሻ አካላት በጋራ በመቀናጀት መስራት ይገባል

NTD

በሲዳማ ክልል አስተናጋጅነት በሀገራችን ለሶስተኛ ጊዜ እየተዘከረ ባለው የአለም ትኩረት የሚሹ የሀሩራማ በሽታዎች ቀንን አስመልክቶ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ ባስተላለፉት መልእክት እንደ ዝሆኔ/ፖዶኮኒዮሲስ፣ ሊንፋቲክ ፊላሪያሲስ፣ ሀይድሮ ሲል፣ ሌሽሚያሲስ የመሳሰሉ የቆላማ እና ሀሩራማ በሽታዎች ለረጅም ዘመን ትኩረት ሳያገኙ በመቆየታቸው ዜጎችን ለተለያዩ አካላዊ፣ ስነ-ልቦናዊ፣ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳቶች እየዳረጉ መሆናቸውን ተናግረው ይህንን ለመቀየር ጥራት ያለው የጤና አገልግሎትን በሁሉም ስፍራ ማዳረስ ረገድ ሁሉም በጤና ዘርፍ እየሰሩ ያሉ አካላት ተገቢ ትኩረት እንዲሰጡ፣ እንዲሁም በጋራ በመቀናጀት እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል። 

የመሀል ሜዳ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል መደበኛ የሕክምና አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።" የሆስፒታሉ ሥራ አስኪያጅ አቶ ወርቅነህ ዘዉዴ 

Mehal Meda

በአሸባሪውና ዘራፊው ቡድን የሕክምና አገልግሎት ያቋረጠው የመሀል ሜዳ ሆስፒታል በዳግማዊ ሚኒልክ ሆስፒታልና በአካባቢው ማህበረሰብ በተደረገለት ድጋፍ የህክምና አገልግሎት መስጠት መጀመሩን የሆስፒታሉ ሥራ አስኪያጅ አቶ ወርቅነህ ዘዉዴ ተናገሩ።


ሆስፒታሉ በተደረገለት የህክምና መገልገያ መሳሪያዎችና የመድኃኒት አቅርቦት ድጋፍ የእናቶችና የህፃናት ጤና አገልግሎት፣ የድንተኛና ጽኑ ሕሙማን አገልግሎት የተመላላሽ ህክምና አገልግሎት በየእለቱ በአማካይ ከ 150 እስከ 200 ታካሚዎች አገልግሎት እየተሰጠ እንደሚገኝ ገልጸው ሙሉ ለሙሉ ሆስፒታሉን ወደ ስራ ለመመለስ ተጨማሪ ድጋፎች እንደሚያስፈልጉ ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል።


በሆስፒተሉ ሲገለገሉ ያገኘናቸው ወ/ሮ አስካለ ገዛኸኝ እና አቶ በልዩ ካሳዬ ተመላላሽ ህክምና ክትትላቸው በመቋረጡ ከፍተኛ ስጋት እንዳሳደረባቸው ገልጸው ሆስፒታሉ አገልግሎት ጀምሮ በማየታቸው መደሰታቸውን ተናግረዋል።