Articles

አስራ ስድስተኛው የቲቢ ምርምር ጉባኤ በሀዋሳ ከተማ ተጀምሯል

TB research

አመታዊ ብሔራዊ የቲቢ ምርምር ጉባኤ በዚህ አስቸጋሪ ወቅት መደረጉ ጠቀሜታው የጎላ ነው ያሉት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር አየለ ተሾመ አገራች ኢትዮጵያ በተከሰተው ጦርነት እና የተለያዩ ግጭቶች ምክንያት በጤና ተቋማት ላይ የደረሰው ውድመቶች እና የጤና ተቋማት መስተጓጎል፤ የህዝብ መፈናቀል፤ የድርቅ መስፋፋት እና በኮቪድ 19 ወረርሽኝ ምክንያቶች በቲቢ በሽታ መከላከል እና ቁጥጥር ላይ የተመዘገቡ ስኬቶች እንዳይቀለበሱ በቁርጠኝነት ልንሰራ ይገባል ብለዋል፡፡ 


በየአመቱ በሚካሄደው የቲቢ ምርምር ጉባኤ ላይ የሚቀርቡ የምርምር ሥራዎች የቲቢ በሽታን በመከላከልና በመቆጣጠር ረገድ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያደረገ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ 
አገራች ኢትዮጵያ የቲቢ በሽታ ስርጭት ለመግታትና ቲቢ ለማጥፋት ዘመናዊ የምርመራ መሳሪያዎችን በጤና ተቋማት በማስገባት አገልግሎቱ ተደራሽ በማድረግና በየአምስት አመቱ የሚተገበር እቅድ በማዘጋጀት እየተሰራ ነው ተብሏል፡፡ 

በህግ ማስከበር እና በህልውና ዘመቻው አስተዋጽኦ ላበረከቱ የጤናው ዘርፍ አካላት ምስጋናና እውቅና ተሰጣቸው

Gratitude and recognition program

በሃገራችን በተካሄደው በህግ ማስከበር እና በህልውና ዘመቻው ላይ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ጤና ተቋማት፣ ጤና ክብካቤ ባለሙያዎችና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጤና ሚኒስቴር እና በኢ.ፌ.ዲ.ሪ መከላከያ ሚኒስቴር በጋራ የተዘጋጀ የምስጋና የእውቅና መርሃ ግብር ተካሄደ፡፡


በፕሮግራሙ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር አብይ አህመድ ባደረጉት ንግግር የጤና ባለሙያዎችና የጤና ክብካቤ ሰራተኞች እንደ ሰው፣ እንደ ኢትዮጵያዊ እና እንደ ሃኪም ሶስት ማንነትን ተላብሳችሁ ለሰራችሁት ታላቅ ገድል ከፍተኛ ምስጋና ይገባችኋል ብለዋል፡፡

286 ሺህ ዶላር የሚገመት የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ ለቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ተደረገ 

Coca-Cola Foundation

ድጋፉን ያደረገው የኮካ ኮላ ኩባንያ የአለም በጎ አድራጎት ክንፍ የሆነው ኮካ ኮላ ፋውንዴሽን ነው፡፡ 


በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ይፋዊ የርክክብ ስነ-ስርአቱ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ የተደረገው ድጋፍ የቅዱስ ጳውሎስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለታካሚዎች የጤና አገልግሎት ለመስጠት ያለውን አቅም ለማሳደግ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል፡፡