Articles

በሀገራችን ያለውን መሰረታዊ የጤና አገልግሎት ፋይናንስ ስርዓት ለማጠናከር የሚያችል አውደ ጥናት ተካሄደ 

basic health care financial system

በቅርቡ የታተመው የላንሴት ግሎባል የጤና ኮሚሽን ሪፖርት ላይ በማተኮር "የህብረተሰብ ጤና ክብካቤ ላይ መዋዕለ ንዋይ በማፍሰስ ሰውን ማስቀደም" በሚል መሪ ቃል የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ በተገኙበት የመጀመሪያ ደረጃ የጤና ክብካቤ ፋይናንስ ላይ ትኩረቱን ያደረገ መድረክ የክልል ጤና ቢሮ ኃላፊዎች የጤና ሚኒስቴር ተጠሪ ተቋማት እንዲሁም የገንዘብ ሚኒስቴር እና አጋር ድርጅቶችን በማካተት አውደ ጥናት አካሄዷል፡፡


በአገራችን በሽታን በመካከልና ጤና ማበልጸግ ፖሊሲን በመቅረጽ የመጀመሪያ ደረጃ የጤና አጠባበቅ ዘዴን ተግባራዊ እየተደረገ እንደሚገኝና የጤና ኤክስቴንሽን መርሃ ግብር ማሻሻያ ፍኖተ ካርታንም በመዘርጋት ሞዴል ወረዳዎችን ለመፍጠር፣ የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድህን ሸፋንን ለማሳደግ እና ሁሉንም የጤና ተቋማት ወደ ከፍተኛ አፈጻጸም ለመቀየር በመላ ሀገሪቱ እየተሰራበት እንደሚገኝ ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ተደሰ በመድረኩ ላይ ተናግረዋል፡፡

የቀዶ ህክምና፣ የድንገተኛና ጽኑ ህክምና አገልግሎት ጥራትንና ተደራሽነትን ለማሻሻል በትኩረት መስራት ያስፈልጋል።

Dr. Ayele Teshome

የጤና ሚኒስቴር ከደብረብርሀን ዩንቨርሲቲ፣ ከስማይል ትሬን (Smile Train) እና ከኬፕ ታውን ዩንቨርሲቲና ጋር በመቀናጀት ለ3 ቀናት በአዲስ አበባ ሲያካሂድ የነበረውን የዓለም የቀዶ ህክምና፣ የድገተኛና ፅኑ ህሙማን ህክምና አገልግሎት የአመራር ክህሎት ዓውደ ርዕይ ተጠናቋል፡፡ 


በጥናታዊ ዓውደ ርዕዩ የማጠቃለያ መርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት የጤና ሚንስቴር ሚንስትር ዲኤታ ዶ/ር አየለ ተሾመ እንደተናገሩት አውደ ርዕዩ በዓለም አቀፍ የቀዶ ሕክምናና የድንገተኛና ጸኑ ህክምና ላይ ትኩረት አድርጎ መወያየቱ የሚደገፍና ትክክለኛው ጊዜ መሆኑን ጠቅሰው እንደ ሃገር የአገልግሎቱን ጥራትና ተደራሽነት ለማስፋፋት የጤና ሚኒስቴር በ5 ዓመቱ እስራቴጂክ ዕቅድ አካቶ በትኩረት እየሰራ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

በኢትዮጵያና በአጎራባች ሀገራት የጤና ስርዓትን  ለማጠናከር የሚያግዙ ስምምነቶችና እርዳታዎች ተደረጉ፡፡

Agreements

የሀገራችን የጤና ስርዓትን በማጠናከር የሀገር ውስጥና ድንበር ተሻጋሪ የጤና በሽታዎችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የበለጠ ተግቶ መስራት እንዲቻል በዛሬው እለት በኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በአውሮፓ ህብረት ድጋፍና በምስራቅ አፍሪካ በየነ-መንግስታት ድርጅት (ኢጋድ)እንዲሁም በዩኖፕስ አስተባባሪነት የኢትዮጵያንና የአጎራባች ሀገራት የጤና ስርዓትና የኮቪድ-19 ምላሽን ለመደገፍ ለኢትዮጵያ የጤና ሚኒስቴር በተደረገው ልዩ ልዩ የጤና አምቡላንሶችና ቁሳቁሶች ርክክብ እና የመግባቢያ ሠነድ ፊርማ ሥነ-ሥርዓት ላይ የጤና ሚኒስትር ክብርት ዶ/ር ሊያ ታደሰ እንደገለጹት የተሻለ ጤናን መኖር የሚቻለው የተሻለ የጤና ሥርዓት ሲገነባ እንደሆነ በአጽንኦት ተናግረዋል፡፡