Articles

የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በ72 ኛው የአፍርካ አህጉር የአለም ጤና ድርጅት መድረክ ላይ እየተሳተፈ ነው።

Dr. Dereje Duguma

ዛሬ በሎሜ ቶጎ የተጀመረዉ 72 ኛው የአፍርካ አህጉር የአለም ጤና ድርጅት መድረክ ላይ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን እየተሳተፈ ይገኛል።  

                         
ይህ 72 ኛው የአፍሪከ አህጉር ከዓለም ጤና ድርጅት ስድስት የአህጉራዊ አስተዳደር አካላት አንዱ ሲሆን 47 አባል ሀገራት ያሉት  የአፍሪካ ክልል ሀገራት የሚወክሉበት  ኮሚቴ ነው፡፡ 


በመድረኩም የአፍርካ የአለም ጤና ንኡስ ኮሚቴዎች እባላት የሚሰየም ሲሆን እኤአ የ2022 የስራ እፈጻጸም እንዲሁም የአፍሪካ ማህበረሰብ ጤና አሁናዊና ቀጣይ  ስትራቴጅክ ጉዳዮች ከአለማችን ማህበረሰብ ጤና ጋር ያለዉ አጠቃላይ ሁኔታ በመድረኩ ቀርበው ምክክርና ውይይት የሚደረግ ይሆናል። 


መድረኩም ለቀጠይ 5 ቀናት በሎሜ ቶጎ የሚቀጥል ይሆናል።

የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ መከላከል እና መቆጣጠር የ2015 እቅድ ማስተዋወቂያ እና የምክክር መድረክ ተካሄደ

Hiwot Solomon

የዘንድሮው አመታዊ አገራዊ የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ መከላከል እና መቆጣጠር እቅድ የክልል እና ከተማ መስተዳድር ጤና ቢሮዎችን እና ኤች.አይ.ቪ/ኤድስ መከላከል እና መቆጣጠር ጽህፈት ቤቶችን ሴክተር መስሪያ ቤቶችን እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላትን በማስተባበር የተዘጋጀ ሲሆን፤ የ2014 በጀት አመት አፈጻጸምን በመገምገም 2015 በጀት አመት እቅድ ዝግጅት የጋራ ለማድረግና ቀጣይ እርምጃዎችን ለማፋጠን ይረዳ ዘንድ የተዘጋጀ የምክክር መድረክ መሆኑን በጤና ሚኒስቴር የበሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ህይወት ሰለሞን ገልጸዋል፡፡

በተለያዩ አካላት ሲመራ የነበረው የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ መከላከል እና መቆጣጠር ስራ አዲስ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት በአንድ እንዲመራ መደረጉ መልካም ነው ያሉት ዳይሬክተሯ፤ በአለም አቀፍ ደረጃ የተቀመጠውን አቅጣጫ በማሳካት የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ ስርጭትን በ2030 ለማስቆም መስራት ይገባል ብለዋል፡፡

የኮቪድ 19 ወረርሽኝን በመከላከልና በመቆጣጠር ረገድ ሚና ለነበራቸው የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ ባለሙያዎች የምስጋና መርሀግብር ተካሄደ።

St Paul

በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ በተዘጋጀዉ ፕሮግራም ላይ የተገኙት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ ባደረጉት ንግግር በሀገራችን ባለፉት ጊዜያት በተከሰቱ የኮቪድ 19 ወረርሽኝ እና ጦርነት በቀዳሚነት ምላሽ በመስጠት ላበረከቱት አስተዋጽዖ አመስግነዋል። የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ኮሌጅ አመራሮች እና ሰራተኞች በዛ አስቸጋሪ ወቅት ዋጋ ከፍለው ላሳዩት ርብርብ ሚኒስቴር መስሪያቤቱ እውቅና እና ምስጋና ያቀርባል ብለዋል።


በዚያ ወረርሽኝ ወቅት የሆስፒታሉ አመራሮች እና ሰራተኞች ቅድሚያ ተነሳሽነት በማሳደር በሚሊኒየም የኮቪድ ማእከል መስዋትነት በመክፈል ጭምር ለሰሩት ስራ እና በሌሎች ክልሎችም ማእከላቱ እንዲስፋፉ በማገዝ ላበረከታችሁት አስተዋጽዎ ምስጋና ይገባችዃል ያሉት ዶክተር ሊያ ትልቅ ስራ እና ሀላፊነትም መወጣት የሚችል አቅም እንዳለን የተገነዘብንበትና የኮራንበት ስራም ነው ብለዋል።