Articles

የኮቪድ 19 ወረርሽኝን በመከላከልና በመቆጣጠር ረገድ ሚና ለነበራቸው የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ ባለሙያዎች የምስጋና መርሀግብር ተካሄደ።

St Paul

በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ በተዘጋጀዉ ፕሮግራም ላይ የተገኙት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ ባደረጉት ንግግር በሀገራችን ባለፉት ጊዜያት በተከሰቱ የኮቪድ 19 ወረርሽኝ እና ጦርነት በቀዳሚነት ምላሽ በመስጠት ላበረከቱት አስተዋጽዖ አመስግነዋል። የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ኮሌጅ አመራሮች እና ሰራተኞች በዛ አስቸጋሪ ወቅት ዋጋ ከፍለው ላሳዩት ርብርብ ሚኒስቴር መስሪያቤቱ እውቅና እና ምስጋና ያቀርባል ብለዋል።


በዚያ ወረርሽኝ ወቅት የሆስፒታሉ አመራሮች እና ሰራተኞች ቅድሚያ ተነሳሽነት በማሳደር በሚሊኒየም የኮቪድ ማእከል መስዋትነት በመክፈል ጭምር ለሰሩት ስራ እና በሌሎች ክልሎችም ማእከላቱ እንዲስፋፉ በማገዝ ላበረከታችሁት አስተዋጽዎ ምስጋና ይገባችዃል ያሉት ዶክተር ሊያ ትልቅ ስራ እና ሀላፊነትም መወጣት የሚችል አቅም እንዳለን የተገነዘብንበትና የኮራንበት ስራም ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ የውስጥ ደዌ ህክምና ማህበር 7ኛው ዓመታዊ ሳይንሳዊ ጉባኤ ተካሄደ

group picture

በእለቱ በክብር እንግድነት የተገኙት የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር አየለ ተሾመ በጉባኤው መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር እንደገለጹት ባለፉት ሁለት አስርት አመታት የኢትዮጵያ ጤና ፖሊሲ በማህበረሰብ ጤና ማጎልበት፣ በሽታ መከላከልና የጤና አገልግሎት ሽፋን ማሻሻል ላይ ትኩረት አደርጎ የተሰራበት እና በዚህም ብዙ ስኬቶች  የተመዘገቡበት እንደነበር የተናገሩ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ግን የተላላፊ በሽታዎች ብቻ ሳይሆኑ ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች እና አደጋዎችም በከፍተኛ ሁኔታ መጨመራቸውን ተከትሎ የከፍተኛ የፈውስ ህክምና ፍላጎትም እንዲሁ የጨመረበት ወቅት በመሆኑ የጤና ሚኒስቴር ለዚሁ ምላሽ በሁሉም የአገሪቱ ክፍሎች የሶስተኛ ደረጃ /tertiary care/  አገልግሎት ተደራሽነትንና ጥራትን ለማሻሻል እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ 

አባቶች፣ የቤተሰብ አባላትና ማህበረሰቡ ለሚያጠቡ እናቶች ትኩረት ሊሰጡ ይገባል

group picture

"ምቹ ሁኔታ ለሚያጠቡ እናቶች፣ እናስተምር፣ እንደግፍ!!" በሚል መሪ ቃል በአለም ለ30ኛ ጊዜ በሃገራችን ደግሞ ለ14ኛ ጊዜ የጡት ማጥባት ሳምንት እየተከበረ ሲሆን ዛሬ በደብረብርሃን ወይንሸት የተፈናቃዮች መጠለያ ከሚገኙ እናቶችና ህጻናት ጋር በአሉ ተከብሯል። 


በጤና ሚኒስቴር ሃገር አቀፍ የስርዓተ ምግብ ፕሮግራም አስተባባሪ የሆኑት ወ/ሮ ህይወት ዳርሰኔ በስነስርዓቱ ላይ እንደ ተናገሩት እናቶች ልጆቻቸውን እስከ ስድስት ወራት ጡት ብቻ ማጥባታቸው የህጻኑን ጤንነት ከመጠበቅና የተስተካከለ እድገት እንዲኖረው ከማስቻሉ ባለፈ ሃገራዊ ጥቅሙ ከፍተኛ ነው ብለዋል። እናቶች በማይመች ሁኔታ ውስጥም ቢሆኑ ለልጆቻቸው የጡት ወተትን መስጠት ማቋረጥ እንደሌለባቸው ለእናቶቹ አስገንዝበው አባቶች፣ የቤተሰብ አባላትና ማህበረሰቡም ለሚያጠቡ እናቶች ትኩረት ሊሰጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።