የስርዓተ ምግብ ትግበራን ለማጠናከር የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች የጋራ የምክክር መድረክ ተካሄደ
በሰቆጣ ቃልኪዳን የተገኙ መልካም ተሞክሮዎችን ለሌሎች የአፍሪካ ሃገራት በማጋራት በአፍሪካ ደረጃ መቀንጨርን ለማስቀረት፣ የሰው ሀብትን ለማሳደግ፣ እና በዘርፉ እድገትን ለማፋጠን አላማ አድርጎ በኢትዮጵያ መንግስት እና በአፍሪካ ልማት ባንክ ትብብር የተባበሩት መንግስታት አጠቃላይ ጉባኤ እየተካሄደ ባለበት በአሜርካ ኒዉዮርክ ከተማ የተዘጋጀ የጎንዮሽ መድረክ ነው።
በመድረኩ ላይ ኢትዮጵያ የመቀንጨር ምጣኔን ከመቀነስ አኳያ እየሰራች ያለውን ዘርፍ ብዙ ትብብርና ምላሽ አጠቃላይ ልምድና በሰቆጣ ቃልኪዳን ስምምነት የተገኙ መልካም ተሞክሮ በኢፌድሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር በክቡር አቶ ደመቀ መኮንን ቀርበዋል።