Articles

“በጎነት ለጤናችን’’በሚል ነፃ የጤና ምርመራ እና የህክምና የበጎ ፍቃድ አገልግሎት በክልሎችና በከተማ መስተዳደሮች ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡

voluntary service

በአገር አቀፍ ደረጃ በአንድ ሳምንት ከመቶ ሺ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የነጻ የጤና ምርመራ እና ህክምና አገልግለት ለመስጠት የተጀመረው  ሰው- ተኮር የበጎ ፈቃድ የተግባር ዘመቻ  በሁሉም ክልሎችና በከተማ መስተዳደሮች በተጠናከረ መልኩ ቀጥሏል፡፡


በዘመቻውም የጤና አጠባበቅ ትምህርትና ምክር አገልግሎት ፣ በተላላፊና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ፣የኮሌራና ሌሎች ውሀ ወለድ በሽታዎች፣ ወባ፣ ኤች አይ ቪ ፣ ቲቪ ፣ ኮቪድ-19፣ የካንሰር ህመምና ሌሎች ትኩረት በሚሹ የጤና ጉዳዮች ላይ ማለትም የደም ግፊት ፣የደም የስኳር መጠን፣ ከአንገት በላይ፣ የአይን፣ የቆዳ፣የስነ ምግብ፣ የአእምሮ ጤና  እና ሌሎች የጤና አገልግሎቶች እየተሰጡ ይገኛሉ፡፡

የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በ72 ኛው የአፍርካ አህጉር የአለም ጤና ድርጅት መድረክ ላይ እየተሳተፈ ነው።

Dr. Dereje Duguma

ዛሬ በሎሜ ቶጎ የተጀመረዉ 72 ኛው የአፍርካ አህጉር የአለም ጤና ድርጅት መድረክ ላይ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን እየተሳተፈ ይገኛል።  

                         
ይህ 72 ኛው የአፍሪከ አህጉር ከዓለም ጤና ድርጅት ስድስት የአህጉራዊ አስተዳደር አካላት አንዱ ሲሆን 47 አባል ሀገራት ያሉት  የአፍሪካ ክልል ሀገራት የሚወክሉበት  ኮሚቴ ነው፡፡ 


በመድረኩም የአፍርካ የአለም ጤና ንኡስ ኮሚቴዎች እባላት የሚሰየም ሲሆን እኤአ የ2022 የስራ እፈጻጸም እንዲሁም የአፍሪካ ማህበረሰብ ጤና አሁናዊና ቀጣይ  ስትራቴጅክ ጉዳዮች ከአለማችን ማህበረሰብ ጤና ጋር ያለዉ አጠቃላይ ሁኔታ በመድረኩ ቀርበው ምክክርና ውይይት የሚደረግ ይሆናል። 


መድረኩም ለቀጠይ 5 ቀናት በሎሜ ቶጎ የሚቀጥል ይሆናል።

የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ መከላከል እና መቆጣጠር የ2015 እቅድ ማስተዋወቂያ እና የምክክር መድረክ ተካሄደ

Hiwot Solomon

የዘንድሮው አመታዊ አገራዊ የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ መከላከል እና መቆጣጠር እቅድ የክልል እና ከተማ መስተዳድር ጤና ቢሮዎችን እና ኤች.አይ.ቪ/ኤድስ መከላከል እና መቆጣጠር ጽህፈት ቤቶችን ሴክተር መስሪያ ቤቶችን እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላትን በማስተባበር የተዘጋጀ ሲሆን፤ የ2014 በጀት አመት አፈጻጸምን በመገምገም 2015 በጀት አመት እቅድ ዝግጅት የጋራ ለማድረግና ቀጣይ እርምጃዎችን ለማፋጠን ይረዳ ዘንድ የተዘጋጀ የምክክር መድረክ መሆኑን በጤና ሚኒስቴር የበሽታዎች መከላከልና መቆጣጠር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ህይወት ሰለሞን ገልጸዋል፡፡

በተለያዩ አካላት ሲመራ የነበረው የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ መከላከል እና መቆጣጠር ስራ አዲስ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት በአንድ እንዲመራ መደረጉ መልካም ነው ያሉት ዳይሬክተሯ፤ በአለም አቀፍ ደረጃ የተቀመጠውን አቅጣጫ በማሳካት የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ ስርጭትን በ2030 ለማስቆም መስራት ይገባል ብለዋል፡፡