Articles

በህግ ማስከበር እና በህልውና ዘመቻው አስተዋጽኦ ላበረከቱ የጤናው ዘርፍ አካላት ምስጋናና እውቅና ተሰጣቸው

Gratitude and recognition program

በሃገራችን በተካሄደው በህግ ማስከበር እና በህልውና ዘመቻው ላይ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ጤና ተቋማት፣ ጤና ክብካቤ ባለሙያዎችና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጤና ሚኒስቴር እና በኢ.ፌ.ዲ.ሪ መከላከያ ሚኒስቴር በጋራ የተዘጋጀ የምስጋና የእውቅና መርሃ ግብር ተካሄደ፡፡


በፕሮግራሙ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር አብይ አህመድ ባደረጉት ንግግር የጤና ባለሙያዎችና የጤና ክብካቤ ሰራተኞች እንደ ሰው፣ እንደ ኢትዮጵያዊ እና እንደ ሃኪም ሶስት ማንነትን ተላብሳችሁ ለሰራችሁት ታላቅ ገድል ከፍተኛ ምስጋና ይገባችኋል ብለዋል፡፡

286 ሺህ ዶላር የሚገመት የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ ለቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ተደረገ 

Coca-Cola Foundation

ድጋፉን ያደረገው የኮካ ኮላ ኩባንያ የአለም በጎ አድራጎት ክንፍ የሆነው ኮካ ኮላ ፋውንዴሽን ነው፡፡ 


በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ይፋዊ የርክክብ ስነ-ስርአቱ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ የተደረገው ድጋፍ የቅዱስ ጳውሎስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለታካሚዎች የጤና አገልግሎት ለመስጠት ያለውን አቅም ለማሳደግ ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል፡፡

በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ምግብን መሠረት ያደረገ የአመጋገብ መመሪያ ይፋ ተደረገ 

Nutrition

የጤና ሚኒስቴር፣ የግብርና ሚኒስቴር፣ የትምህርት ሚኒስቴር እና አጋር አካላት በኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስተባባሪነት በጋራ ያዘጋጁት በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነውን ምግብን መሠረት ያደረገ የአመጋገብ መመሪያ (Food-Based Dietary Guidelines (FBDG's) በዛሬው ዕለት ይፋ ሆኗል።