Articles

በኢትዮጵያ ሁለተኛ የሆነው የካንሰር ህክምና ጨረር አገልግሎት መስጫ ማዕከል ተመረቀ

Inauguration

በኢትዮጵያ በየአመቱ ከሰባ ሺ በላይ ዜጎች በተለያየ አይነት የካንሰር በሽታዎች እንደሚጠቁ ጥናቶች ያሳያሉ፡፡ ለእነዚህ የማህበረሰብ ክፍሎች የጨረር ህክምና አገልግሎት ሲሰጥ የቆየው የጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ብቻ ነበር፡፡


በዛሬው ዕለት የተመረቀውና አገልግሎት እየሰጠ የሚገኘው የጅማ ዩንቨርስቲ ሆስፒታል የጨረር ህክምና ማዕከል በከፍተኛ ወጪ መዘጋጀቱና አገልግሎት መጀመሩ በጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ላይ ብቻ ተወስኖ የቆየው የጨረር ህክምና አገልግሎት ጫናን በመቀነስ በህክምናው ተደራሽነት ላይ ትልቅ አስተዋጽኦ ያደርጋል ተብሏል፡፡

ሰማሪታንስ ፐርስ ኢንተርናሽናል ሪልፍ የእርዳታ ድርጅት ለኢትዮጵያ 12.5 ሚሊዮን ብር የሚገመት የህክምና ቁሳቁስና ግብአት ድጋፍ አደረገ

Samaritan’s Purse

የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ በቦሌ አየር ማረፊያ ተገኝተው ከሰማሪታንስ ፐርስ ኢንተርናሽናል ሪልፍ ካንትሪ ዳይሬክተር ሪል ላን ድጋፉን ተረክበዋል፡፡ ዶ/ር ሊያ በርክክብ ስነስርዓቱ ጊዜ እንደተናገሩት መቀመጫውን በአሜሪካ አገር ያደረገው የሰማሪታንስ ፐርስ ኢንተርናሽናል ሪልፍ በኢትዮጵያ ከንጹህ የመጠጥ ውኃ አቅርቦትና ሳኒቴሽን፣ ከኮቪድ-19 እና በሌሎች የድንገተኛ ምላሽ ድጋፍ ስራዎችን ሲሰራ የቆየ ተቋም መሆኑን አንስተው አሁን 12.5 ሚሊዮን ብር የሚያወጡ የህክምና ግብአትና መሳሪያዎች ድጋፍ ማድረጉን ገልጸዋል፡፡ 

በውጭ ሀገር ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ አትዮጵያውያ የተሰባሰቡ መድኃኒቶች ጥቃት ለተፈጸመባቸው የህክምና ተቋማት ማሰራጨት ተጀመረ።

Donation

የጤና ሚኒስቴር ከዲያስፖራው ማህበረሰብ የተደረጉ ድጋፎችን በተቀናጀ መልኩ እንዲሰበሰብ፣ እንዲለይና በጦርነቱ ለተጎዱ ጤና ተቋማት ከተደለደለ በኋላ ስርጭቱ እንዲከናወን በተሰጠው አቅጣጫ መሰረት የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ለየጤና ተቋማቱ ከየካቲት 04/2014 ዓ.ም ጀምሮ ስርጭት እያከናወነ ሲሆን  እስካሁንም ሸዋሮቢት፣ በአጣዮ ሆስፒታል እና ጤና ጣቢያ፣ በከሚሴ ሆስፒታል፣ በኮንቦልቻ ሆስፒታል እና ጤና ጣቢያ፣ በደሴ ሆስፒታል፣ በሰኞ ገበያ ጤና ጣቢያ፣ እና በቦሩ ሜዳ ሆስፒታል ድጋፉን ማድረስ ተችሏል። በመቀጠልም አፋር ክልልን ጨምሮ በተቀሩ አከባቢዎች የሚሰራጭ ይሆናል።