በኢትዮጵያ ሁለተኛ የሆነው የካንሰር ህክምና ጨረር አገልግሎት መስጫ ማዕከል ተመረቀ
በኢትዮጵያ በየአመቱ ከሰባ ሺ በላይ ዜጎች በተለያየ አይነት የካንሰር በሽታዎች እንደሚጠቁ ጥናቶች ያሳያሉ፡፡ ለእነዚህ የማህበረሰብ ክፍሎች የጨረር ህክምና አገልግሎት ሲሰጥ የቆየው የጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ብቻ ነበር፡፡
በዛሬው ዕለት የተመረቀውና አገልግሎት እየሰጠ የሚገኘው የጅማ ዩንቨርስቲ ሆስፒታል የጨረር ህክምና ማዕከል በከፍተኛ ወጪ መዘጋጀቱና አገልግሎት መጀመሩ በጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ላይ ብቻ ተወስኖ የቆየው የጨረር ህክምና አገልግሎት ጫናን በመቀነስ በህክምናው ተደራሽነት ላይ ትልቅ አስተዋጽኦ ያደርጋል ተብሏል፡፡