Articles

የአውሮፓ ህብረት አባል አገራት ለኢትዮጵያ የኮቪድ-19 ክትባት ድጋፍ አደርጉ!

EU

ኢትዮጵያ የኮቪድ-19 ክትባት ድጋፍ ከአውሮፓ ህብረት አገራት ተረከበች። 


ድጋፍ ያደረጉ አገራት ሰድስት ሲሆኑ እነሱም ፈርንሳይ (6746 400)፣ ፊላንድ(1699200) ዴንማርክ (1560000)፣ ግሪክ (1346400) ጣልያን (1264110 ) ስዊድን (480690) ዶዝሰ በአጠቃላይ (13 096 800 ዶዝስ) የኮቪድ-19 ክትባት ድጋፍ ማግኘቷ ታውቀዋል። 


በርክክብ ስነስርኣቱ የአገራቱ አምባሳደሮች፣ የኢምባሲ ተወካዮች፣ የዩኒሴፍ ተጠሪዎች የተገኙት ሲሆን የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ ጋር ውይይት አድርገዋል፡፡ 
በመድረኩ ላይ ዶክተር ሊያ እንዳሉት የተደረገው ድጋፍ የክትባት አቅርቦትን እንደሚያሳድግ ገልጸው ይህም ለበሽታው መግታትና መከላከል ትልቅ ፋይዳ እንደሚኖረው ተናግረዋል። 

የኢትዬጵያ ሕብረተሠብ ጤና ኢንስቲትዩት ለኢ.ፌ.ዴ.ሪ ሀገር መከላከያ ሰራዊት 5 ሚሊዮን ብር እና ከ200 ሺ ብር በላይ የሚገመት አልባሳት ድጋፍ ተደረገ

Defense Force

በርክክቡ ወቅት የጤና ሚኒስቴር ዶ/ር ሊያ ታደሰ ባስተላለፉት መልእክት የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ለሀገር ህልውና እና እያደረገ ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን ገልፀው የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ይህን ታሳቢ በማድረግ ያደረገውን ድጋፍ አመስግነዋል። ይህም ድጋፍ 5 ሚሊዬን ብር እና ከ200 ሺ በላይ የሚገመቱ አንሶላዎች፣ ቢጃማና ነጠላ ጫማዎች መሆኑንም ገልፀዋል።

የመከላከያ ሠራዊት ምንስትር ዴኤታ ወ/ሮ ማርታ ሊዊጂ በበኩላቸው የጤናው ዘርፍ በዚህ ፈታኝ ወቅት ለሀገር እያደረገ ያለው አበርክቶ እጅግ ከፍተኛ መሆኑን ገልፀው አሁንም በገንዘብና በዓይነት በኢትዬጵያ ሕብረተሠብ ጤና ኢንስቲትዩት የመጣው ድጋፍ ለመከላከያ ሠራዊት የሚሰጠው አገልግሎት እጅግ ከፍተኛ መሆኑን በመግለጽ በመከላከያ ሰራዊት ስም አመስግነዋል።

የጤና ሚኒስቴር በአለታ ወንዶ ከተማ በአነስተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ አባወራዎች ያስገነባቸው  ቤቶችን ለተጠቃሚዎች አስረከበ 

Aleta Wondo

የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ በክረምት በጎ አገልግሎት በአለታ ወንዶ ከተማ በዝቅተኛ ኑሮ ለሚገኙ ስድስት አባወራዎች/እማወራዎች ያስገነባቸውን ቤቶች ለተጠቃሚዎች ያስረከቡ ሲሆን በክረምት በጎ አገልግሎት የጤና ሚኒስቴር ችግኞችን የመትከል እና አቅመ ደካሞችን የማገዝ ስራን ሲሰራ እንደነበር አስታውሰው በአለታ ወንዶ ከተማም ምሳሌ መሆን የሚችል ስራ መሰራቱን ተናግረዋል። ቤቶቹም መሰረታዊ መገልገያ ቁሳቁስ የተሟላላቸው ሲሆን ድጋፉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። 


ድጋፍ የተደረገላቸው ግለሰቦችም በሰጡት አስተያየት መጠለያ ማጣት እጅግ አስቸጋሪ ህይወት እንዲመሩ እንደዳረጋቸው ሆኖም ጤና ሚኒስቴር  እንደደረሰላቸው እና ተስፋቸውን እንዳለመለመ ገልጸው ምስጋናቸውን አቅርበዋል።