የአውሮፓ ህብረት አባል አገራት ለኢትዮጵያ የኮቪድ-19 ክትባት ድጋፍ አደርጉ!
ኢትዮጵያ የኮቪድ-19 ክትባት ድጋፍ ከአውሮፓ ህብረት አገራት ተረከበች።
ድጋፍ ያደረጉ አገራት ሰድስት ሲሆኑ እነሱም ፈርንሳይ (6746 400)፣ ፊላንድ(1699200) ዴንማርክ (1560000)፣ ግሪክ (1346400) ጣልያን (1264110 ) ስዊድን (480690) ዶዝሰ በአጠቃላይ (13 096 800 ዶዝስ) የኮቪድ-19 ክትባት ድጋፍ ማግኘቷ ታውቀዋል።
በርክክብ ስነስርኣቱ የአገራቱ አምባሳደሮች፣ የኢምባሲ ተወካዮች፣ የዩኒሴፍ ተጠሪዎች የተገኙት ሲሆን የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ ጋር ውይይት አድርገዋል፡፡
በመድረኩ ላይ ዶክተር ሊያ እንዳሉት የተደረገው ድጋፍ የክትባት አቅርቦትን እንደሚያሳድግ ገልጸው ይህም ለበሽታው መግታትና መከላከል ትልቅ ፋይዳ እንደሚኖረው ተናግረዋል።