Articles

የኮቪድ 19ን ለመከላከልና ለመቆጣጠር እንዲሁም የወደሙ ተቋማትን መልሶ ለማቋቋም የሚያግዝ ሰው ሰራሽ መተንፈሻ መሳሪያ ድጋፍ ርክክብ ተደረገ

Delivery

ግምታቸው 30 ሚሊዮን ብር የሚሆን 100 ሰው ሰራሽ መተንፈሻ መሳሪያዎች የኮቪድ 19ን ለመከላከልና ለመቆጣጠር እንዲሁም የወደሙ ተቋማትን መልሶ ለማቋቋም የሚያግዝ ሰው ሰራሽ መተንፈሻ መሳሪያ ድጋፍ ለጤና ሚኒስቴር ተደርጓል፡፡

 
ድጋፉን ለጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ  ያስረከቡት የሞደርን ኢ.ቲ.ኤች አውት ሶርስ ፒ.ኤል.ሲ ተወካይ የሆኑት አቶ ታዲዮስ ተፈራ፤ ድጋፉ የተደረገው በኮቪድ የተጠቁ ዜጎችን ለመርዳት ታስቦ መሆኑን ገልጸው ድጋፋቸው የሚቀጥል መሆኑን ተናግረዋል፡፡

 
 የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ ፣ ድጋፉን ያደረጉትን ድርጅቶች አመስግነው፤ መሳሪያዎቹ በጽኑ ህሙማን ማገገሚያ የሚገኙ ታካሚዎችን ለመርዳት ከፍተኛ እገዛ እንደሚያደርጉ ገልጸው ድጋፋቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል።

"እናቶች በጤና ተቋማት በሰለጠኑ ባለሙያዎች እንዲወልዱ ሁሉም የድርሻውን መወጣት አለበት።"  ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ

Dr. Dereje Duguma

የጤናማ እናትነት ወር "በማንኛውም ሁኔታ ከወሊድ በኋላ በደም መፍሰስ ምክንያት የሚከሰተውን የእናቶችን ሞት እጅ ለእጅ ተያይዘን እንግታ" በሚል መሪ ቃል በአለም ለ35ኛ በሀገራችን ደግሞ ለ16ኛ ጊዜ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ አስተባባሪነት በአበበች ጎበና የእናቶችና ህፃናት ሆስፒታል ተከብሯል፡፡ 


የጤና ሚኒስቴር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ በዓሉን አስመልክተው ባደረጉት ንግግር በሀገራችን ከእናቶች ሞት ጋር ተያይዞ በተደረገው ጥናት በዓመት ከሚሞቱት እናቶች በተለይ 50 በመቶ የሚሆኑት ከደም መፍሰስ ጋር በተያያዘ ምክንያት መሆኑን ገልፀው እናቶች በጤና ተቋማት በሰለጠኑ ባለሙያዎች እንዲወልዱ ሁሉም የድርሻውን መወጣት አለበት ብለዋል፡፡ ለዚህም የሃይማኖት አባቶች፣ የሚዲያ ባለሙያዎች፣ የኪነጥበብ ሰዎች፣ በየደረጃው ያሉ አመራሮች፣ የጤና ባለሙያዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ግንዛቤ በመፍጠር እናቶች በህክምና ተቋም እንዲወልዱ እንዲያበረታቱ አሳስበዋል፡፡

በጦርነት እና በተለያዩ ግጭቶች ምክንያት ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎች የስነ አዕምሮ እና የስነ ልቦና ህክምና  ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል በጤና ሚኒስቴርና በሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር የተዘጋጀ የዘርፈ ብዙ ምላሽ እቅድ ይፋ ተደረገ

ministers

በተለያዩ ክልሎች በጦርነት እና በተፈጠሩ ግጭቶች ለተፈናቀሉና ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎች የተቀናጀ  የስነ አዕምሮ እና የስነ ልቦና ህክምና ምላሽ  በመስጠት እየተደረገ ያለውን ድጋፍ ይበልጥ ለማጠናከርና ፈጣን ለማድረግ የጤና ሚኒስቴር እና የሴቶችና  ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር በጋራ ያዘጋጁት እቅድ ለባለድርሻ አካላት በኢትዮጵያ የህረተሰብ ጤና ኢንስትቲዩት የህብረተሰብ ጤና አደጋዎች የመልሶ ማቋቋምና ሪዚሊየንስ ዳይሬክተር በሆኑት በዶ/ር ያረጋል ፉፋ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።


በቅንጅታዊ  ርብርቡ የስነ አዕምሮ ፣  የስነ ልቦና እና የማህበራዊ ስራዎች እንዲሁም ለተለያዩ ባለድርሻ አካላት ግንዛቤ የመፍጠር ተግባራት እንደሚከናወኑ በእቅዱ የተካተቱ ዝርዝር አላማዎች ያሳያሉ፡፡