Articles

ጠንካራ የፋይናንስና ፍትሃዊ የጤና ስርዓቶች ጥራት ላለው የጤና አገልግሎት

discussion

በጅግጅጋ በሚካሄደው የጤናው ዘርፍ ልማት ጉባኤ የሁለተኛ ቀን ውሎ ተሳታፊዎች በተለያዩ ጤና ጉዳዮች ላይ የፓናል ውይይት አካሂደዋል፡፡
የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሠ እና የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሰሃረላ አብዱላሂ የተገኙበት የፓናል ውይይት የጤና ፋይናንስን እና ፍትሃዊነትን ማሻሻል ላይ ትኩረት ያደረገ ነበር፡፡


የጤና ፋይናንስ ስርዓቱን አስመልክቶ በቀረበው ፓናል ውይይት ከሃገር አቀፍና ከዓለም አቀፍ ድርጅቶች የሃብት ማሰባሰብ ስራዎች የተሰሩ ሲሆን መንግስት ከጠቅላላው በጀት ውስጥ 13 ነጥብ 2 በመቶ የሚሆነውን ለጤናው ዘርፍ እንዲመደብ ለማድረግ ተችሏል፡፡  
የግሉን የጤና ዘርፍና የመንግስትን ትብብር ለማጠናከር በተሰራው ስራ የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ በተለይም የጤና ግብአቶች ምርትና ተርሸሪ ኬር ላይ እንዲጨምር ማድረግ መቻሉ በውይይቱ ተነስቷል፡፡ 

በጂግጂጋ ዩኒሸርሲቲ ሼህ ሀሰን የቦሬ ሪፈራል ሆሰፒታል የሚገኘው የኩላሊት እጥበት ማእከል እና የጂግጂጋ የደምና ቲሹ ባንክ በዛሬው እለት በጤና ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ተጎብኝቷል

visit

የጤና ሚኒስቴር ከፍተኛ የስራ አመራሮች ከክልሉ የጤና ቢሮ የስራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን በሆስፒታሉ የሚገኙ የMRI ክፍልን፣ የኩላሊት እጥበት ህክምና ማእከልን፣ የደምና ቲሹ ባንክን የጎበኙ ሲሆን በተለይ የከተማዋ ህብረተሰብና ባለሀብቶችን በማሳተፍ የተቋቋመው የኩላሊት እጥበት ህክምና ማእከል አገልግሎት አሰጣጥ ተዘዋዉረው ተመልክተዋል።


የኩላሊት እጥበት ህክምና ማእከሉ ከሱማሌ ና ከአካባቢው ለሚመጡ ተካሚዎች በተመጣጣኝ ዋጋ አገልግሎት ተደራሸ እያደረገ እንደሆነ በጉብኝቱ ተገልጿል። በዚህም በ2013 ዓ.ም ለ724 ታካሚዎች አገልግሎቱን መስጠት  እንደተቻለ ተገልጿል።


በተለይ የጂግጂጋ የደምና ቲሹ ባንክ የመረጃ ስርአቱን ዲጂታላይዝ የማድረግ ስራን ዶ/ር ሊያ ታደሰ በጉኝቱ ወቅት በይፋ ያሰጀመሩ ሲሆን የምርመራ ሂደቱን በአዉቶሜሸን በመታገዝ እየተከናወነ እንደሚገኝ ተመልክተዋል። 

ተንቀሳቃሽ የጤና ቡድን አገልግሎት ተደራሽ ላልሆኑ የአርብቶ አደር የህብረተሰብ ክፍሎች

jigjiga

ከጥቅምት 19_21/2014 ዓ.ም በሶማል ክልል ጅግጅጋ ከተማ የሚካሄደው የጤናው ዘርፍ ልማት የምክክር ጉባኤ በመጀመሪያ ቀን ውሎ በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች ያሉ የጤና አገልግሎት አሰጣጥ ተሞክሮዎችን ምልከታ በማድረግ ጀምሯል።


በጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ እና በሶማሌ ክልል ጤና ቢሮ  ምክትል ሃላፊ ወ/ሮ ሀዋ ሱሌማን የተመራው ቡድን ከጅግጅጋ ከተማ 55 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በምትገኘው ጎልጃኖ ወረዳ መልካዳ ካስ ቀበሌ የመስክ ጉብኝት አካሂዷል።


በጉብኝቱም ተግባራዊ በመደረግ ላይ ያለው የተንቀሳቃሽ የጤና ቡድን አገልግሎት የስራ ተሞክሮ ታይቷል። በሶማሌ ክልል በ29 ቡድኖች የተንቀሳቃሽ የጤና አገልግሎት እየተሰጠ ሲሆን እያንዳንዱ ቡድን ለስድስት ቀበሌዎች አገልግሎት ይሰጣል።