በአማራ እና አፋር ክልሎች ጉዳት ለደረሰባቸው የሆስፒታል ላብራቶሪዎችን መልሶ ለማቋቋም የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ ተደረገ
6.5 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ የላብራቶሪ ህክምና ቁሳቁስ ድጋፍን ያደረገው የኦሃዮ ስቴት ግሎባል ዋን ሄልዝ ሲሆን በጦርነት ጉዳት የደረሰባቸው የህክምና ተቋማትን መልሶ ለማቋቋም የሚውል መሆኑ ተገልጿል፡፡
የጤናው ዘርፍ በጦርነቱ ከፍተኛ ውድመት ያሰተናገደ ዘርፍ መሆኑን የገለጹት የጤና ሚኒስቴር ሚንስትር ዴዔታ ዶ/ር አየለ ተሸመ፤ የተደረገው ድጋፍ ያጋጠሙትን ችግሮች ለመቅረፍ የሚረዳ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
የላብራቶሪ ህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ የተደረገላቸው ተቋማት የተሟላ የህክምና አገልግሎት ለመስጠት እንዲችሉ እየተደረገ ያለውን ጥረት የሚደገፍ መሆኑን በመግለጽ ስለተደረገው ድጋፍ በጤና ሚኒስቴር፣ ድጋፍ በተደረገላቸው ተቋማት እና በተቋማቱ አገልግሎት በሚያገኙ ማህበረሰቦች ስም ምስጋና አቅርበዋል፡፡