Articles

የቀዶ ህክምና፣ የድንገተኛና ጽኑ ህክምና አገልግሎት ጥራትንና ተደራሽነትን ለማሻሻል በትኩረት መስራት ያስፈልጋል።

Dr. Ayele Teshome

የጤና ሚኒስቴር ከደብረብርሀን ዩንቨርሲቲ፣ ከስማይል ትሬን (Smile Train) እና ከኬፕ ታውን ዩንቨርሲቲና ጋር በመቀናጀት ለ3 ቀናት በአዲስ አበባ ሲያካሂድ የነበረውን የዓለም የቀዶ ህክምና፣ የድገተኛና ፅኑ ህሙማን ህክምና አገልግሎት የአመራር ክህሎት ዓውደ ርዕይ ተጠናቋል፡፡ 


በጥናታዊ ዓውደ ርዕዩ የማጠቃለያ መርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት የጤና ሚንስቴር ሚንስትር ዲኤታ ዶ/ር አየለ ተሾመ እንደተናገሩት አውደ ርዕዩ በዓለም አቀፍ የቀዶ ሕክምናና የድንገተኛና ጸኑ ህክምና ላይ ትኩረት አድርጎ መወያየቱ የሚደገፍና ትክክለኛው ጊዜ መሆኑን ጠቅሰው እንደ ሃገር የአገልግሎቱን ጥራትና ተደራሽነት ለማስፋፋት የጤና ሚኒስቴር በ5 ዓመቱ እስራቴጂክ ዕቅድ አካቶ በትኩረት እየሰራ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

በኢትዮጵያና በአጎራባች ሀገራት የጤና ስርዓትን  ለማጠናከር የሚያግዙ ስምምነቶችና እርዳታዎች ተደረጉ፡፡

Agreements

የሀገራችን የጤና ስርዓትን በማጠናከር የሀገር ውስጥና ድንበር ተሻጋሪ የጤና በሽታዎችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የበለጠ ተግቶ መስራት እንዲቻል በዛሬው እለት በኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በአውሮፓ ህብረት ድጋፍና በምስራቅ አፍሪካ በየነ-መንግስታት ድርጅት (ኢጋድ)እንዲሁም በዩኖፕስ አስተባባሪነት የኢትዮጵያንና የአጎራባች ሀገራት የጤና ስርዓትና የኮቪድ-19 ምላሽን ለመደገፍ ለኢትዮጵያ የጤና ሚኒስቴር በተደረገው ልዩ ልዩ የጤና አምቡላንሶችና ቁሳቁሶች ርክክብ እና የመግባቢያ ሠነድ ፊርማ ሥነ-ሥርዓት ላይ የጤና ሚኒስትር ክብርት ዶ/ር ሊያ ታደሰ እንደገለጹት የተሻለ ጤናን መኖር የሚቻለው የተሻለ የጤና ሥርዓት ሲገነባ እንደሆነ በአጽንኦት ተናግረዋል፡፡

በጤና ኤክስቴንሽን መርሃ-ግብር ትግበራ የአጋር ድርጅቶች ሚና ውጤታማ ነበር

Health Extension

በጤና ኤክስቴንሽን መርሃ-ግብር ትግበራ በርካታ የጤና አገልግሎቶች ማህበረሰቡን ተደራሸ ለማድረግ የአጋር ድርጅቶች ሚና ውጤታማ እንደነበር እና እንደ ሃገር አመርቂ የጤና ውጤቶች የተመዘገበበት እንደሆነ ተጠቁሟል፡፡ 


በፕሮግራሙ  ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ድጉማ እንደገለጹት የጤና ስርዓታችን በተለይም የእናቶችና ህጻናት ጤና አገልግሎትና የመጀመሪያ ደረጃ የጤና አገልግሎት ተጠቃሚ የሆነበት የጄ ኤስ አይ/ኤል10ኬ 10 ኪሎ ሜትር/JSI L10K 10K/ ባለፉት 14 ዓመታት የነበረው አገልግሎት ውጤታማ እንደነበር አንስተው ከጤና ሚኒስቴር ጋር በቅንጅት በመስራት ለተገኘው ውጤትና ድጋፍ ላደረጉ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበው። በቀጣይም ይህ ፕሮጅክት ቀጣይነት እንዲኖረው ድጋፍ የሚያደርጉ አካላት በትብብር ውጤታማ ስራ ለመስራት ድጋፋቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡