Articles

"በግሎባል ፈንድ የሚተገበሩ ፕሮግራሞች ውጤት ተኮር በመሆናቸው ሁሉም አካል በትኩረት ሊሰራባቸው ይገባል።" የጤና ሚኒስትር ዴኤታ - ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ

Dr. Dereje Duguma

ግሎባል ፉንድ ግራንት ፕሮግራም ትግበራ ሂደቶችን የመገምገም እና እስካሁን በተያዙ እቅዶች አፈጻጸም ላይ ያተኮረ ግምገማ  ዛሬ በጤና ሚኒስቴር መሰብሰቢያ አዳራሽ ተካሂዷል፡፡ 


የግምገማ መድረኩ በጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ የተመራ ሲሆን ትኩረቱንም እስካሁን ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከግሎባል ፈንድ በተገኝው የፋይናንስ ድጋፍ በጤናው ዘረፍ የተከናወኑ ዝርዝር ስራዎች ቀድሞ ከታቀደው እቅድ አኳያ አሁናዊ ደረጃው ምን እንደሚመስል እና የእቅድ አተገባበሩ ምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝ የተገመገመበት ነው።


የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ በግምገማ መድረኩ እንደተናገሩት በግሎባል ፈንድ የሚተገበሩ ፕሮጀክቶች ውጤት ተኮር በመሆናቸው ሁሉም አካል በትኩረት ሊሰራባቸው እንደሚገባ  አንስተዋል፡፡ 

የኮቪድ-19 መከላከያ ክትባት ተደራሽነትን ለማሳደግ ከአጋር ድርጅት ኃላፊዎችና ተወካዮች ጋር ውይይት ተደረገ

Discussion

የኮቪድ-19 መከላከያ ክትባት ተደራሽነትና ሽፋንን አስመልክቶ በጤና ሚኒስቴር በየደረጃው የሚገኙ ኃላፊዎች፣የጋቪ፣ የዩኒሲኤፍ እና የአለም ጤና ድርጅት ተወካዮችና ኃላፊዎች በተገኙበት ውይይት ተደረጓል፡፡ 


ባለፉ በርካታ ዓመታት የክትባት አገልግሎት ተደራሽነት ላይ በቁርጠንነት ድጋፍ ሲያደርጉ የቆዩ አጋር ድርጅቶችን በማመስገን ንግግራችውን የጀመሩት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ ሲሆኑ በተለይ የኮቪድ ወረርሽኝን ከመግታትና አፋጣኝ ምላሽ ከመስጠት ረገድ ባለድርሻ አካላት የነበራቸው ሚና ከፍተኛ ነበር ብለዋል፡፡