Articles

በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በጋምቤላ ክልል የአቅመ ደካሞችን ቤት የማደስ ስራ ተጀመረ 

Dr. Lia Tadesse

በ2014 በጀት ዓመት በጤና ሚኒስቴር አስተባ ባሪነት ተጠሪ ተቋማትን ባከተተ መንገድ የተለያዩ የክረምት በጎፍቃድ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛል።


 የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የአቅመ ደካሞችን ቤት የማደስ ማስጀመሪያ መርኃ ግብር ዛሬ በጋምቤላ ከተማ፣ የአቅመ ደካማ ቤቶች እድሳትን አስጀመሩ። በዚህም የ 5 አቅመ ደካሞች ቤት ሙሉ በሙሉ የሚታደስ ይሆናል።


በክልሉ የአቅመ ደካማ ወገኖችንን ቤት ከማደስ ፕሮግራም ማስጀመር በተጨማሪ  የጋምቤላ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ  ሆስፒታል  የድንገተኛ ህክምና አገልግሎት አሰጣጥ፣ በክልሉ የሚገነባው ሪጅናል ላብራቶሪ ግንባታ ሒደት፣ እንዲሁም አሻራችን ለትውልዳችን በሚል መሪ መልክት  በጋምቤላ ከተማ ጤና ጣቢያ የችግኝ ተከላ ተካሒዷል። 


 በመርሀ ግብሩም በክልሉ በዝቅተኛ ገቢ ከሚተዳደሩ የአቅመ ደካማ ልጆች ለ400 ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስና ድጋፍ ተደርጓል። 

የእናት ጡት ወተት የህይወት ምግብ!

Dr. MESSERET ZELALEM

“ምቹ ሁኔታ ለሚያጠቡ እናቶች፤ እናስተምር፤ እንደግፍ!!” በሚል መሪ ቃል የዘንድሮው የጡት ማጥባት ሣምንት በዓለም ለሰላሳኛ በሀገራችን ደግሞ ለአስራ አራተኛ ጊዜ እየተከበረ ነው፡፡

የሥርዓተ ምግብ ችግሮች በዓለም ላይ በየዓመቱ ወደ አምስት ሚሊዮን ሕፃናት ህመምና ሞት ምክንያት ነው ያሉት የጤና ሚኒስቴር የእናቶች ህፃናት እና የስርዓት ምግብ ዳይሬክተር ዶ/ር መሰረት ዘላለም ከፅንስ ጀምሮ እስከ ሁለት ዓመት ዕድሜ ባለው ጊዜ ማስተካከል ካልተቻለ መቀንጨር እና ሌሎች የምግብ አለመመጣጠን ችግሮች ሊከሰት እና በቀጣዩ የእድሜ ክልል ከትውልድ ወደ ትውልድ ሊተላለፍ የሚችል አመጋገብ ችግር ይሆናል ብለዋል።

ኦሀዮ ስቴት ዩኒቨርሲቲ ግሎባል ዋን ሄልዝ ፕሮግራም  በሰሜኑ ክፍል በነበረው ጦረነት ለተጎዱ የጤና ተቋማት ድጋፍ አደረገ

Ohio State University

በዛሬው እለት የተደረገው ድጋፍ 9 ሚሊዮን ብር የሚያወጡ የላብራቶሪ እቃዎች መሆናቸው ማወቅ የተቻለ ሲሆኑ ድጋፉ የተደረገው በአማራ እና በአፋር በክልል ለሚገኙ ስድስት ሆስፒታሎች ሲሆን በስድስቱ ሆስፒታሎች ውስጥ ላሉ የላብራቶሪ ክፍሎችን መልሶ ለማደረጃት የሚረዳ ድጋፍ ነው፡፡


በርክክብ ስነስርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ እንዳሉት በአገራቱ የነበረው ጦርነት የጤና ተቋማትን ማውደሙን ተከትሎ መልሶ ለማቋቋም በተደረገው ርብርብ ሁሉም ሆስፒታሎች ወደ ስራ እንዲገቡ መደረጉን አንስተዋል፡፡ ኦሀዮ ስቴት ዩኒቨርሲቲ ግሎባል ዋን  ሄልዝ ፕሮግራም ለዚህ ችግር ትኩረት በመስጠት  የሆስፒታሎችን ላብራቶሪዎች ሙሉ ለሙሉ ለመደገፍ መቻሉን ዶክተር ሊያ የተናገሩ ሲሆን በቴክኒክም የማጠናከር ስራ እየሰራ መሆኑንም ነው የገለጹት፡፡