Articles

ከግሎባል ፈንድ በተገኘ 453 ሚልዮን የአሜርካ ዶላር ድጋፍ የቲቢ፣ የኤች አይ ቪ፣ የወባ በሽታዎችን በመከላከልና በመቆጣጠር እንዲሁም የጤና ስርአትን በማጠናከር ረገድ  የተመዘገቡ ውጤቶች አበረታች ናቸው።

Global Fund

ፕሮጀክቶች የተከናወኑት አገራችን በተለያዩ ችግሮች ማለትም ኮቪድ 19፣ የተለያዩ ግጭቶች እና ድርቅ ውስጥ በነበርችበት ጊዜ ቢሆንም፣ ፈንዱን በመጠቀም አበረታች ውጤቶችን ለማስመዝገብ ተችላል። የተገኙ ውጤቶችን ለማስፋፋትና ያጋጠሙ ችግሮችን በዘላቅነት ለመፍታት የሚያስችል አውደ ጥናት ተካሂዷል።

በአውደ ጥናቱ ላይ የጤና ሚኒስቴር፣ የክልል ጤና ቢሮና የኤጀንሲ ኃላፊዎች፣ የድጋፍ ባለሙያዎች እና ሌሎች ጉዳዩ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

በመድረኩ ላይ የተገኙት የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጄ ዱጉማ፣ ግሎባል ፈንድ የኢትዮጵያ መንግስት የጤናውን ስርዓት በማጠናከር በተለይም የኤች አይ ቪ፣ የወባ እና የቲቢ በሽታዎችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በሚተገበሩ ስራዎች ላይ ለሚያከናውናቸው የድጋፍ ተግባራት እና ላበረከተው አስተዋጽኦ ምስጋናቸውን  አቅርበዋል፡፡

"ማህበራዊ የባህሪ ለውጥ ለዘላቂ ልማት" በሚል መሪ ቃል 3ኛው ሀገር አቀፍ የማህበራዊና የባህሪ ለውጥ ጉባኤ በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡

Dr. Mekdes Daba

ጤና ሚኒሰቴር ከኢትዮጵያ ጤና ትምህርትና ፕሮሞሽን ባለሙያዎች ማህበር እንዲሁም ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር ሶስተኛውን ሃገር አቀፍ የማህበራዊ እና ባህሪ ለውጥ ጉባዔ “የማህበራዊ እና ባህሪ ለውጥ ተግባራት ለዘላቂ የጤና ልማት” በሚል መሪ ቃል ከ13 አለም አቀፍ አገራት ከመጡ የዘርፉ ባለሙያዎችን ጨምሮ 400 በላይ ተሳታፊዎች በተገኙበት በአዲስ አባባ በማካሄድ ላይ ይገኛል፡፡

ዩኤስኤአይዲ( USAID) 156 የጅን ኤክስፕርት ማሽኖች ድጋፍ ለጤና ሚኒስቴር አድርጓል

USAID

ድጋፉ ሶስት ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ወጪ የተደረገበት ሲሆን የቲቢ ፈጣን ሞለኪውላር ምርመራ በማድረግ የቲቢ በሽታን በፍጥነት ለማግኘት የሚያስችል ቴን ከለርድ የጂን ኤክስፐርት ማሽኖች ድጋፍ መሆኑ ታውቋል፡፡ በድጋፍ የተገኙት የጂን ኤክስፐርት ማሽኖቹ በተለይ ለተጎጂ ክልሎች እና የቲቢ ስርጭት ላለባቸው አካባቢዎች ላይ ላሉ ጤና ተቋማት እንደሚተላለፉ ተገልጿል።

የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ድጉማ በድጋፉ የርክክብ ስነስርዓት ላይ እንደተናገሩት የጤና ሚኒስቴር የሳንባ ነቀርሳን ለማጥፋት አዲስ የ7 ዓመታት ስትራቴጂክ እቅድ ማዘጋጀቱንና ዩኤስኤአይዲ ኢትዮጵያ በአዲሱ ስትራቴጂክ ዕቅድ ውስጥ ቁልፍ ሚና እንደነበረው ጠቅሰው ለእቅዱ ስኬት መረጃን መሰረት ባደረገ፤ ውጤታማ በሆነ መንገድ መተግበርን ይጠይቃል ብሏል።