በጂግጂጋ ዩኒሸርሲቲ ሼህ ሀሰን የቦሬ ሪፈራል ሆሰፒታል የሚገኘው የኩላሊት እጥበት ማእከል እና የጂግጂጋ የደምና ቲሹ ባንክ በዛሬው እለት በጤና ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ተጎብኝቷል

visit

የጤና ሚኒስቴር ከፍተኛ የስራ አመራሮች ከክልሉ የጤና ቢሮ የስራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን በሆስፒታሉ የሚገኙ የMRI ክፍልን፣ የኩላሊት እጥበት ህክምና ማእከልን፣ የደምና ቲሹ ባንክን የጎበኙ ሲሆን በተለይ የከተማዋ ህብረተሰብና ባለሀብቶችን በማሳተፍ የተቋቋመው የኩላሊት እጥበት ህክምና ማእከል አገልግሎት አሰጣጥ ተዘዋዉረው ተመልክተዋል።


የኩላሊት እጥበት ህክምና ማእከሉ ከሱማሌ ና ከአካባቢው ለሚመጡ ተካሚዎች በተመጣጣኝ ዋጋ አገልግሎት ተደራሸ እያደረገ እንደሆነ በጉብኝቱ ተገልጿል። በዚህም በ2013 ዓ.ም ለ724 ታካሚዎች አገልግሎቱን መስጠት  እንደተቻለ ተገልጿል።


በተለይ የጂግጂጋ የደምና ቲሹ ባንክ የመረጃ ስርአቱን ዲጂታላይዝ የማድረግ ስራን ዶ/ር ሊያ ታደሰ በጉኝቱ ወቅት በይፋ ያሰጀመሩ ሲሆን የምርመራ ሂደቱን በአዉቶሜሸን በመታገዝ እየተከናወነ እንደሚገኝ ተመልክተዋል። 

ተንቀሳቃሽ የጤና ቡድን አገልግሎት ተደራሽ ላልሆኑ የአርብቶ አደር የህብረተሰብ ክፍሎች

jigjiga

ከጥቅምት 19_21/2014 ዓ.ም በሶማል ክልል ጅግጅጋ ከተማ የሚካሄደው የጤናው ዘርፍ ልማት የምክክር ጉባኤ በመጀመሪያ ቀን ውሎ በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች ያሉ የጤና አገልግሎት አሰጣጥ ተሞክሮዎችን ምልከታ በማድረግ ጀምሯል።


በጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ እና በሶማሌ ክልል ጤና ቢሮ  ምክትል ሃላፊ ወ/ሮ ሀዋ ሱሌማን የተመራው ቡድን ከጅግጅጋ ከተማ 55 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በምትገኘው ጎልጃኖ ወረዳ መልካዳ ካስ ቀበሌ የመስክ ጉብኝት አካሂዷል።


በጉብኝቱም ተግባራዊ በመደረግ ላይ ያለው የተንቀሳቃሽ የጤና ቡድን አገልግሎት የስራ ተሞክሮ ታይቷል። በሶማሌ ክልል በ29 ቡድኖች የተንቀሳቃሽ የጤና አገልግሎት እየተሰጠ ሲሆን እያንዳንዱ ቡድን ለስድስት ቀበሌዎች አገልግሎት ይሰጣል።

በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የጥፋት ቡድኑ ባደረሰው ጉዳት ተፈናቅለው ባህርዳር ለሚገኙ ወገኖችና በክልሉ ውስጥ  ጉዳት ለደረሰባቸው  15 ጤና ጣቢያዎች  ድጋፍ ተደረገ 

Amhara

በጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴአታ ወ/ሮ ሠሐረላ አብዱላሂ የተመራ ከጤና ሚኒስቴር፤ ፌዴራል ሆስፒታሎችና ከተጠሪ ተቋማትና ከግሉ ዘርፍ የተውጣጣ ቡድን በአማራ ክልል በባህርዳር ከተማ በህውሃት የጥፋት ቡድን ባደረሰባቸው ጉዳት ተፈናቅለው ጉዳት የደረሰባቸው ዜጎችን ጎብኝቷል።

 
ቡድኑ ከደሴና ኮምቦልቻ አከባቢ በፀጥታው ችግር ምክንያት ተፋናቅለው በባህርዳር ከተማ በዘንዘልማ የተፈናቃዮች መጠለያ የሚገኙትን የጎበኙ ሲሆን በከተማው አስራ አራት ሺ አምስት መቶ ሃያ ሁለት ሺህ የሚሆኑ ተፈናቃይ ወገኖች እንደሚገኙና በመጠለያ ቦታው አራት ሺ ሁለት መቶ ሃምሳ ሁለት ተፈናቃዮች የሚገኙ መሆኑ ታውቋል፡፡ ለተፈናቀሉ ወገኖች የጤና አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ የክልሉ ጤና ቢሮ ባለሙያዎችን መድቦ ክሊኒክ የከፈተላቸው ሲሆን ከተፈናቀሉ የጤና ባለሙያዎች እና አጋር ድርጅቶች ጋር በመቀናጀት የህክምና አገልግሎትና የማልኑትሪሽን ችግር ልየታ ስራ እየተሰራ መሆኑን መመልከት ተችለዋል። 

የጡት ካንሰር ግንዛቤ ወር የክብርት ፕሬዚደንት መልዕክት

HE the President

የጥቅምት ወር የጡት ካንሰር ግንዛቤ ወር ነው። የጡት ካንሰር ሴቶችን በከፍተኛ  ደረጃ ያጠቃል። በአገራችን ታካሚዎች ወደ ጤና ተቋም የሚሄዱት ዘግይተው ነው። የሚታዩ ምልክቶችን በጊዜ ለመለየት ቅድመ ምርመራ እንዲደረግ የሚመለከታቸው ሁሉ በቂ ግንዛቤ ሊይዙ ይገባል። ይህ ባለመሆኑ ብዙዎችን አጥተናል።


ከአገራችን የተለያዩ ክፍሎች ለጨረርና ለኪሞ ሕክምና የሚመጡ ሴት ወገኖቻችን መጠለያ ቦታ ስለሌላቸው ለተጨማሪ ችግር ይጋለጣሉ። ችግሩን ለመቅረፍ ለእነዚህ ሕሙማን ማረፍያ ቦታ በማዘገጀት፣  ወደ ሆስፒታል በማመላለስ፣ መድሃኒት ግዢ ላይ በመደገፍ ወዘተ . . . ከሚሠሩ ድርጅቶች መካከል "ፒንክ ሃውዝ" የተባለውን በቅርብ ጎብኝቻለሁ። ይህንንና ተመሳሳይ ተቋሟችን በመደገፍ ሴቶች በጊዜ ከተደረሰበት ሊታከም በሚችል በሽታ እንዳይጎዱ እናድርግ።

"የጤና መድህን አባላትን ቁጥር በማሳደግ የዜጎችን ተጠቃሚነት የማረጋገጡ ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል" የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሠ

lia

አገር አቀፍ የጤና መድህን አገልግሎት የ2013 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና የ2014 ዓ.ም ዕቅድ ግምገማ ጉባኤ ማጠቃለያ ላይ ተገኝተው የስራ አቅጣጫ የሰጡት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሠ እንደተናገሩት የጤና መድህን አባላትን ቁጥር በማሳደግ የዜጎችን ተጠቃሚነት የማረጋገጡ ስራ በ2014 በጀት ዓመትም ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡


የጤና መድህን አባላትን ቁጥር በማሳደግና ዘላቂነት ያለው የፋይናንስ ስርዓትን በመፍጠር በጤና ተቋማት ላይ የሚነሱ ችግሮችን ለመቅረፍ እንደሚረዳ የገለጹት ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሠ ይህንን ለማሳካትም ከላይ እስከታች ያለው የጤና መዋቅር አመራር በመደጋገፍና በቅንጅት መንፈስ ሊሰራ ይገባልም ብለዋል፡፡

ፖሊዮን ጨርሶ ለማጥፋት የሚያስችል የክትባት ዘመቻ  በይፋ ተጀመረ

Dr. Dereje Duguma

ከፖሊዮ ነጻ የሆነ አለም እንፍጠር በሚል መሪ ቃል በአገር አቀፍ ደረጃ በሲዳማ ክልል በአዋሳ ከተማ እና በደቡብ ክልል ጌዲዮ ዞን ዲላ ከተማ የክትባት ዘመቻ መርሀግብር ያስጀመሩት የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ  በመርሀግብሩ እንደተናገሩት የጤና ሚኒስቴር ፖሊዮን ለማጥፋት በመደበኛ ክትባትና በዘመቻ በሚሰጥ ክትባት ከሀገራችን  ለማጥፋት ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው።


ባለፉት አመታትም በተከናወነው ስራ ፖሊዮን ማጥፋት ተችሎ የነበረ ሲሆን በአሁኑ ወቅት  በተለያዩ አከባቢዎች  እየታየ ያለውን የልጅነት ልምሻ በሽታ ለማጥፋትም እስከ ጤና ኬላ በተዘረጋ መዋቅር እና ከአጋር አካላት ጋር በተቀናጀ አሰራር እየተተገበረ መሆኑን ተናግረው  ይህም መንግስት ለሕጻናት ጤና መሻሻል ትልቅ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ ማሳያ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ 

በጤናው ዘርፍ የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት የሰጡ የአዲስ አበባ ወጣቶች እውቅና ተሰጣቸው

youth

የጤና ሚኒስቴር ከአዲስ አበባ ወጣቶች በጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ቢሮ ጋር በመተባበር በጤናው ዘርፍ የክረምት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት የእውቅና አሰጣጥ መርሃ ግብር በዛሬው እለት አካሂዷል፡፡ 


እውቅናውን  የተሰጣቸው የአዲስ አበባ ወጣቶች ሲሆኑ በቅዱስ አማኑኤል የአዕምሮ ስፔሻላይዝድ  ሆስፒታል፣ በአለርት ማእከል፣ በቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል፣ በጥሩነሽ ቤልጂንግ  ሆስፒታል፣ በካቲት 12 ሜዲካል ኮሌጅ፣ በራስ ደስታ ሆስፒታል እና በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒዬም ሜዲካል ኮሌጅ ወስጥ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሲሰጡ የቆዩ ወጣቶች ናቸው፡፡


የእውቅና አሰጣጥ መድረኩን በንግግር የከፈቱት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር አየለ ተሾመ እንደ ጤና ሴክትር ብዙ ነገሮችን በገንዘብ እጥረት ምክንያት ማሳካት በማንችልበት አገር ውስጥ የበጎ ፈቃደኝነት አገልግሎት  መሰረታዊ ጉዳይ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡

በአሜሪካ መንግስት 453,600 ዶዝ ጆንሰን ጆንሰን ኮቪድ19 ክትባቶች ለኢትዮጵያ ድጋፍ ተደረገ 

donation


ከአሜሪካ መንግስት ዓለም አቀፍ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ስርጭትን ለመከላከል 453,600 ዶዝ ጆንሰን ጆንሰን ኮቪድ19 ክትባቶች ለኢትዮጵያ ድጋፍ ተደረገ ፡፡


በርክክቡ ስነ ስርዓት ላይ የተገኙት የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሰሐረላ አብዱላሒ ባደረጉት ንግግር ከአሜሪካ መንግስት ወደ ኢትዮጵያ የገባው ክትባት ለአራተኛ ዙር እንደሆነ እና በዛሬው እለትም 453,600 ዶዝ ጆንሰን ጆንሰን ኮቪድ19 ክትባቶችን መረከባቸውን እንዲሁም በቀጣይ ተጨማሪ 504 ሺ ክትባቶች እንደሚገቡ ይፋ አድርገውዋል፡፡

የጤና ሚኒስቴር ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በደቡብ ወሎ ኮምቦልቻ ከተማ በመገኘት ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው በጊዜያዊ መጠለያ የሚገኙ ዜጎች የሚያገኙትን የጤና አገልግሎት በተመለከተ ምልከታ አካሄዱ 

Dr Dereje

በጥፋት ሀይሎች ለተጎዱ የጤና ተቋማትና በችግሩ የተፈናቀሉ ዜጎችን ጤንነት ለመጠበቅ  የሚደረጉ ድጋፎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተገልጻል።
የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ እና የሚኒስቴሩ የእናቶች እና ህጻናት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር  ዶ/ር መሰረት ዘላለም ከኮንቦልቻ ከተማ ከንቲባ እና ከጤና መምሪያ የስራ ሃላፊዎች ጋር በመሆን በመጠለያ የሚገኙ ዜጎችን ጎብኝተዋል።


በጉብኝቱ ወቅትም ከዩኤንኤፍፒኤ (UNFPA) በድጋፍ የተገኙ 590ሺ ዶላር ግምት ያላቸው የተለያዩ የንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁሶችን፣ የስነ ተዋልዶ ኪቶችን፣ የኮቪድ መከላከያ ግብዓቶች የተረከቡ ሲሆን በርክክቡ ወቅትም ዶ/ር ደረጀ  ዱጉማ እንደተናገሩት  የጥፋት ሀይሎች በጤና ተቋማት ያደረሱትን ውድመት እና ዝርፍያ እንደዚሁም የበርካታ ዜጎችን ከቤት ንብረታቸው መፈናቀላቸውን በዚህም ለተለያዩ የጤና ጉዳቶች መጋለጠቸውን ጠቅስው በዩኤንኤፍፒኤ (UNFPA) በኩል የተደረገው ድጋፍ በአስፈላጊ  ወቅት እና አካባቢ መደረጉንም ገልጸዋል።